ፋብሪካችን ሞሓ የለስላሳ መጠጦች ኢንዳስትሪ አክስዩን ማህበር መቐለ ፔፕሲ ኮላ ፋብሪካዉ በኣረንጋዴ ዘርፍ ለተሰማሩት ባለመያ በጨረታ አወዳድሮ ከትእምት ቢሮ ኣከባቢ ጀምሮ እስከ መቐለ ዩኒቨርስቲ ኣሪድ በር ካምፓስ ያለዉን ጎዳና በኣረንጋዴ ልማት ግሪነሪ ለማልማት ይፈልጋል።

ፋብሪካ ልስሉስ መስተ ሞሃ

1 ተጫራቾች በዘርፉ የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ : የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፊኬት: ቫት ተመዝጋቢ መሆኑ የሚያረጋግጥ ሰርተፊኬት እና ቲን ምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

2 ተጫራቾች ለጨረታዉ ማስከበሪያ ለጥሩ የጠቅላላ የጨረታ ዋጋ 2% የገንዘብ ክፍያ ማዘዣ CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል ።

3 ተጫራቾች የሚቀርቡትን ዋጋ ቫት ያካተተ ሙሆኑን እና አለመሆኑን በግልፅ መቀመጥ ይኖርባቸዋል። ይህ ካልሆነ ግን ዋጋዉ ቫትን ያካተተ መሆኑ ታሳቢ ይደረጋል።

4 የጨረታዉ ዝርዝር ሰነድ ከድርጅቱ ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 12 ድረስ በመምጣት እና ብር 50.00 በመክፈል ሰነዱን መውሰድ ይቻላል።

5 ተጫረቾች ዋጋቸዉ በታሸገ ኢንቨሎፕ ይህን ጨረታ ከወጣበት ግዜ ጀምሮ እስከ 17/02/2012 ዓ/ም በስራ ቀንና ሰዓት ኣክሱም ሆቴል ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ዋና ቢሮኣችን ድረስ በመምጣት ለዚሁ ተብሎ በተዘገጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል። በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ እና የሰነዱ ማሽግያ ፖስታ ተጫራቾች ህጋዊ ማህተምና እና ፊርማ መኖር ይኖርበታል።

6 የጨረታ ሳጥኑ 17/02/2012 ዓ/ም ከቀኑ 8:15 የሚታሸግ ሲሆን ከዚሁ ሰዓት ባኃላ የጨረታ ሰነድ የሚመጣ ተቀባይነት ኣይኖረዉም።

7 ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት/ ባልተገኙበትም 17/02/2012 ዓ/ም ከቀኑ ልክ 8:30 በፋብሪካዉ የግዥና ክምችት መምሪያ ቢሮ ወስጥ ይከፈታል።

8 ተጫራቾች በዚህ ጨረታ ላይ ያሸነፋቸዉ የእቃ ዓይነቶች ማሸነፋቸዉ እንደተነገራቸዉ በ45 ቀናት ወስጥ እቃዎችን የማስረከብ ግዴታ ይኖርባቸዋል።ይህ ሳይሆን ሲቀር ግን ያስያዘዉ የዉል የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ካለ ምንም ቅድመ ሆኔታ ለድርጅቱ ገቢ ይሆናል።

9 ማንኛዉም ተጫራች ጨረታዉ ከተከፈተ ባኃላ ጨረታዉን መሰረዝ ኣይችልም።

10 ስርዝ ድልዝ የሆነ የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረዉም።

11 ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በማንኛዉም ግዜ ጨረታዉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo