የሰቲት ሑመራ ዕቅድና ፋይናንስ ፅህፈት ቤት ለ2012 በጀት ዓመት ለተለያዩ አገልግሎት የሚውል ንብረት በግልፅ ጨረታ ኣወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ቤት ፅሕፈት ትልምን ፋይናንስን ከተማ ሰቲት ሑመራ

ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርት የምታሟሉ አቅራቢዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል፡፡

1 በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑ ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ።

2 ከመንግስት ግዠና ንብረት አስተዳደር በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ተመዝጋቢ የሆነ።

3 ተጫራቾች የግብር ከፋይ ቁጥር /TIN/ ያላቸውና የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችል፡፡

4 የነሐሴ 2011 ዓ.ም ወይም መስከረም ወር 2011 ዓ.ም ቫት ድክሌር ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችል፡፡

5ተጫራቾች ለተወዳደሩበት ግዥ ንብረት የ6ት ወር /ስድስት ወር/ ዋስትና መስጠት የሚችል፡፡

6 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ እንደ ተጫራቹ ምርጫ በጥሬ ገንዘብ ወይም CPO ማስያዝ የሚችል።

6.1 ከሎት አንድ ያሉ ዝርዝር ዓይነት ንብረቶች የፅህፈት መሳሪያዎች ለሎት አንድ 40000 ብር /ኣርባ ሺ ብር/

6.2 ሎት ሁለት ኣላቂ የፅዳት እቃዎች  25000ብር /አምስት ሺ ብር/

6.3 ሎት ሶስት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች 35000 ብር /ሳላሳ ኣምስት ሺ  ብር/

6.4 ሎት አራት ፈሪኒቸር የቢሮ ዕቃዎች  ለሎት አራት 5,000 ብር /ኣምስትሺ ብር/

6.5 ሎት ኣምስት የተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎች እና ተሽከርካሪ መግዣ 15000 ብር /አስራ አምስት ሺ ብር/

6.6  ሎት ስድስት የስፖርት ትጥቕ እቃዎች 35000 ብር /ሳላሳ ኣምስት ሺ ብር/

6.7 ሎት ሰባት የህትመት እቃዎች 3000 ብር/ ሰስት ሺ/

6.8 ሎት ስምንት የሚዚቃ መሳርያ እቃዎች 3000 ሰዎስት ሺ ለብቻው በፖስታ ታሽጎ ፖስታው ላይ ማህተም፣ ፊርማ ስምና አድራሻ አድርጎ ማስያዝ የሚችል፡፡

7 ተጫራቾች በጨረታ ያሸነፈው ዝርዝር ንብረት በራሳቸው ትራንስፖርት በትግራይ ክልል በምዕራባዊ ዞን ሰቲት ሁመራ ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት ማስረከብ የሚችሉ።

8 ተጫራቾች የሚጫረቱበት ዋጋ በግልፅ ኦርጅናል የጨረታ ሰነድ ላይ ሞልተው በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ከ 13/01/2012 እስከ 27/01/2012 ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት /15/ ቀናት ተከታታይ ቀናት ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

9 ጽህፈት ቤቱ 20% በውል ላይ መጨመርም መቀነስም ይችላል፡፡ ጨረታ ሰነዱ በሁመራ ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት ግዢ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ቁጥር 25 በመምጣት 100.00 ብር በመክፈል መግዛት ይችላል፡፡

10 መስሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ላይ ዋጋ ሞልቶ የድርጅቱ ህጋዊ ማህተምና፣ ፊርማ ፣አድራሻ፣ ስም፣ ስልክ ቁጥር አድርጎ የማያቀርብ ተጫራች ከጨረታ ውጪ ይሆናል።

11 ተጫራቾች የሚጫረቱበት የመጫረቻ ሰነድ አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ለየብቻቸው ሆኖ መቅረብ ይኖርበታል። በተጨማሪም ለየብቻው የታሸገ ሆኖ በእያንዳንዱ ፖስታ ላይ የተጫራቾች ህጋዊ ማህተምና ፣ፊርማ ፣አድራሻ፣ ስም፣ ስልክ ቁጥር በማድረግ ሶስቱም ፖስታዎች በአንድ ትልቅ ፖስታ በማሸግ በትልቁ ፖስታ ህጋዊ ማህተምና ፣ፊርማ ፣አድራሻ፣ስም፣ ስልክ ቁጥር በማድረግ ማቅረብ ይኖርበታል።

12 ተጫራቶች የሚሞሉት ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለው በጎኑ ፊርማ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን ያለማድረግ ከጨረታ ውጪ ይሆናል፡፡

13 የሚገዙ የግዥ ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፍኬሽን / ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዘዋል ይመልከቱት፡፡

14 ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ታሽጎ ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በከተማ ሰቲት ሑመራ ዕቅድና ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 25 ይከፈታል። ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ያለመገኘት የጨረታውን ሂደት አያስተጓጉልም።

15 የጨረታው ዋጋ ፀንቶ የሚቆይበት 45 ቀናት ይሆናል፡፡

16 ተጫራቾች የሚሞሉት ዋጋ ከነ ቫቱ መሆኑ እና አለመሆኑ ማመላከት አለባቸው።

17 ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች እቃውን በ 15 ተከታታይ ቀናት ማስረከብ ይኖርበታል።

18 ጽህፈት ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0344480062/63 መደወል ትችላላችሁ።

የሰቲት ሑመራ ዕቅድና ፋይናንስ ፅህፈት ቤት

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo