የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2011 ዓ/ም በጀት አመት የሚያገለግል የውሃ ማጣሪያ ኬሚካል (ክሎሪን) (Calcium Hypochlorite) ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

ቤት ፅሕፈትና ግልጋሎት ቀረብ ማይ ከተማ መቐለ

1 የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው

2 ቫት የተመዘገቡና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ

3 የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ ለእያንዳንዱ ሎት 200 /ሁለት መቶ/በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ፡፡

4 ጨረታ ዶክሜንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ፡፡

5 ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን 2011 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

6 ሁሉም ተጫራቾች 35,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ በCPO፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ፣ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡

7 ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈጽመው መቅረብ አለባቸው፡፡

8 በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም፡፡

9 የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በ CPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል

10 በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ

11 ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣው የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም፡፡

12.ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው፡፡

13 ጽ/ቤቱ ጨረታውን እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

14 የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት

15 ቴክኒካል አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም

16 ፋይናንሻል አንድ ኦሪጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል፡፡

17 ፅ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- ትግራይ መቐለ ስልክ ቁጥር፡-0344407335/0914755845

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo