የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የእርሻ መገልገያ መሣሪያዎች ፣የማንጎና አቮካዶ ዘር ፣ ፀረ ተባይ ኬሚካል፣ ጋብዮን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ

ጨረታ ማስታወቂያ ጨረታ 

ቁጥር 23/2011 

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የተለያዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ማለትም፡

  • ሎት 1 የእርሻ መገልገያ መሣሪያዎች 
  • ሎት 2 የማንጎና አቮካዶ ዘር 
  • ሎት 3. ፀረ ተባይ ኬሚካል 
  • ሎተ 4 ጋብዮን 

በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፤ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ደኩመንት ለእያንዳንዱየማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል:: 

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት የVAT ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይ ነት መለያ ቁጥር (TIN) እና ያለፈው ወር ቫት (VAT) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት፣ 
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በCPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፤ 
  • ጨረታው ግንቦት 16 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ይከፈታል፡፡ 
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው 

ለተጨማሪ ማብራሪያ

በስልክ ቁጥር ፦ 0344403663/0344404346  ወይም በፋክስ ቁጥር 0344409971/ 0344403663 መጠየቅ ይቻላል፡፡ 

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር 

ልማት ቢሮ 

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo