በትግራይ ክልል ትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ የግዥና ንብረት አስተዳደር ለ2011 በጀት ዓመት ጀኔሬተር በአገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

ኤጀንሲ መራከቢ ሓፋሽ ትግራይ

1 የ2011ዓ/ም ዕድሳት የተደረገለት የንግድ ስራ ፍቃድ፣ የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ፣ የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት መጋቢት ወር የቫት ዲክላሬሽን፣ ቲን ምዝገባ ወረቀት ማቅረብ ኣለባቸው ።

2 መስፈርቶቹን የሚያሟሉ ሁሉም ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 (አስራ አምስት ) ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ የግዥና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 105 ከ14/08/2011ዓ/ም እስከ 28/8/2011ዓ/ም 11:30 በስራ ሰአት ሰነዱ መግዛት ይችላሉ።

3 ጨረታው የሚዘጋበት የመጨረሻ ቀን 29/08/2011 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በተመሳሳይ ቀን ጠዋት 4:30 ቢሮ ቁጥር 105 ይከፈታል።

የጨረታ ማስከበሪያ /ዋስትና/ በተጫራቾች ምርጫ መሰረት ከሚከተሉት ዓይነቶች አንዱ ሊሆን ይችላል።

ሀ. በህግ ከታወቀ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (un conditional bank guarantee)

ለ. በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና

ሐ. በታወቀ ባንክ የተረጋገጠ የገንዘብ ክፍያ ማዘዣ (CPO) ሆኖ ብር 100,500.00 (አንድ መቶ ሺ አምስት መቶ ብር ) ማቅረብ ኣለባቸው።

4 የሚያስፈልግ የዶክመንት ብዛት ቴክኒካል ኦርጅናል ዶክመንት ከነ 2 ኮፒ እና ፋይናንሻል ኦርጅናል ዶክመንት ከነ 2 ኮፒ ለየብቻቸው በፖስታ በማሸግ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።

5 ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ያሉትን ቅፆች በትክክል በመሙላት፣ በእያንዳንዱ የሰነዱ ገፅ ፊርማ እና የድርጅቱ ማሕተም ማድረግ ኣለባቸው።

6 ድርጅታችን ትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ይህ ጨረታ በማንኛውም ጊዜ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ይሁን በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ:- ትግራይ ብዙሁን መገናኛ ኤጀንሲ መርሲ ትምህርት ቤት አጠገብ ቢሮ ቁጥር:-05 ግዥና ንብረት አስተዳደር

ስልክ ቁጥር፡- 034-2-40-63-80

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo