የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መቐለ ቅ/ጽ/ቤት ድርጅቶች የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች፣ የፅዳት እቃዎች፣ የኤሌክትሮኒክስና የICT እቃዎች፣ የሰራተኞች ደንብ ልብስ፣ የቢሮ መገልገያ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል

በዓል መዚ ልማዓት እቶት ኢትዮጵያ
  •  ሎት አንድ- የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች
  • ሎት ሁለት- የፅዳት እቃዎች
  • ሎት ሶስት- የኤሌክትሮኒክስና የ ICT እቃዎች
  •  ሎት አራት- የሰራተኞች ደንብ ልብስ
  • ሎት አምስት- የቢሮ መገልገያ እቃዎች

1 ህጋዊ ጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ

2 የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የእቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ

3 ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለሥልጣን የተሰጠ ማቅረብ የሚችል

4 ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት

5 የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ ብር 5,000፣ ለሎት ሁለት ብር 3,000.00፣ ለሎት ሶስት ብር 10,000 እና ሎት አራት 3,000.00 ፣ ሎት አምስት 10,000.00 በባንክ በተመሰከረለት ቼክ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ (Garantty) ዋስትና ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል።

6 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ አጠገብ የሚገኘው የትግራይ ክልል አካል ጉዳተኞች ማህበር ህንፃ ከሚገኘው የቅ/ፅ/ቤት የግዥና ፋይናንስ ቡድን ግራውንድ ላይ ቢሮ ቁጥር 37 በመቀረብ መግዛት ይችላሉ።

7 ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ህዳር 25/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ በመስሪያ ቤቱ አዳራሽ ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 34 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

8 የጨረታው አሸናፊ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) CPO በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል።

9 መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

10 ተጫራቾች ዋጋው ከነቫቱ መሙላት ይጠበቅባቸዋል።

11 ስልክ ቁጥር 0344-411005/0919068385/0914777061 ፋክስ ቁጥር 0344-407309

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo