የትግራይ ልማት ማህበር በመደባይ ዛና : ላዕላይ ማይጨዉና ታሕታይ ማይጨዉ ወረዳዎች የትምህርትና የጤና ተቆማት በኣስር ሎቶች በመከፋፈል ማስራት ይፈልጋል በዚህ መሰረት

ማሕበር ልምዓት ትግራይ

1 ደረጃዉ GC/BC-4 : GC/BC-5 ከዝያ በላይ የሁኑ የ2010 ዓ/ም የኮንስትራክሽን ፍቃዳቸዉና የንግድ ስራ ፈቃዳቸዉ ያሳደሱ : በኮንስትራክሽን ኣቅራቢነት ሰርትፍኬት ያላቸዉ : የቫት ሰርተፍኬት : የቲን ሰርትፍኬትና የመጨረሻ ወር የቫት ዲክላሬሽን የሚቀርቡ ቴክኒካል ዶክመንት ጋር ተያይዝ ካልቀረበ ከዉድድር ወጭ ይሆናል

2 የጨረታዉ ማስከበሪያ ዋስትና በኢትዩጰያ ብሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸዉ የታወቁ ባንኮች 100, 000.00 (ኣንድ መቶ ሺ ብር) : 50, 000.00 (ኣምሳ ሺ ብር) ብሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

3 ተጫራቾች ለሚሰሩት የህነፃ ፕሮጀክት ሳይት ከተረከቡበት ቀን ጀምሮ በ210 (ሁለት መቶ አስር) ተከታተይ ቀናት አጠናቆ ማስረከብ የሚችሉ

4 የጨረታዉ ዶክመንት 8/03/2010ዓም ጀምሮ እስከ 29/03/2010 ዓም አስፈላጊዉን ዶክመንት በመያዝ የማይመለስ ብር 500 (ኣምስት መቶ) በመክፍል ከትግራይ ልማት ማህበር ዋና ፅቤት ቢሮ ቁጥር 435 መዉሰድ ይችላሉ

5 የጨረታዉ ሰነድ በተጫራቾች መመርያ መሰረት ተሞልቶ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክመንቶች ኦርጅናሉና ሁለት ፎቶ ኮፒዎች ሲፒኦ ለየብቻቸዉ በሰም ታሽጎዉ በአንድ ትልቅ ፖስታ ዉስጥ ተከተወና በላይ ላይ ለሚጫረቱት ፕረጀክት ስም በሚታይ ቀለም ፅፈዉ በሁሉም ዶክመንት ላይ ተፈርሞበትና ( አጠቃላይ ላይ ተፈርሞበትና ህጋዊ የሆነ ማህተም በመምታት እስከ 29/03/2010 ዓም ከቀኑ 3:30 ሰዓት በትግራይ ልማት ማህበር ዋናዉ ፅ/ቤት ለዚሁ አገልግሎት የተዘጋጀዉ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል

6 ኣንድ ተጫራቾች መግዛትም ሆነ መወዳደር የሚችሉ ለኣንድ ፕሮጀክት ብቻ ነዉ ከኣንድ በላይ ፕሮጀክት ከ ት.ል.ማ ወስዶ ይህ ጨረታ ሰነድ ኣየር ላይ እስክዋለበት ቀን ድረስ የፕሮጀክቱ ፊዛካል ኣፈፃፀም 70% በታች የሆነ የስራ ተቆራጭ የጨረታ ዶክመንት ምግዛትም ሆነ መወዳደር ኣይችልም

7 ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸዉ ባሉበት 29/03/2010 ዓ/ም ከቀኑ 4:00 በተጠቀሰዉ ቦታ ይከፈታል

8 ኣስሪዉ ፅ/ቤት የተሻላ መንገድ ካገኘ በጨረታዉ ኣይገደድም

9 ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 034 440 68 40 መጠየቅ ይቻላል

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo