በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት - መቐለ ለ 2013 በጀት ዓመት ለ ኢንስቲትዩቱ መኪኖች አገልግሎት የሚውሉ የመኪና ጎማ ፣ በዉስን ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ኢንስቲትዩት ቴክኖሎጂ ኢትዩጵያ

1 በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱም በዘመኑ የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።

2 የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርቲፍኬት ማቅረብ የሚችል ወይም በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብሳይት የተመዘገበ።

3 የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) የተመዘገበና የምዝገባ ሰርቲፍኬት ማቅረብ የሚችል፡፡

4 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል።

5 ለጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) ------ ብር 8,000.00  የመኪና ጎማ 7.50*16 ብዛት 25 የመኪና ጎማ 195*15 ብዛት 05

6 በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል።

7 ማንኛውም ተጫራቾች ለአንድ ሎት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ለዚሁ የተዘጋጀ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።

8 ማንኛውም ተጫራቾች ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢተዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት - መቐለ ዋና ግቢ ቢሮ ቁጥር 219 መውሰድ ይችላሉ።

9 ጨረታዉነሃሴ 25/2012 ወጥቶ  እስከ 15ኛው ቀን መስከረም 04/2013  3፡30 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ተብሎ የተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።

10 ጨረታው መስከረም 04ቀን/2013 ጠዋት 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልፅ ይከፈታል።

11 ኢንስቲትዩቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 09 14 74 93 89  ደውሎ ማነጋገር የሚቻል መሆኑ በማሳሰብ ጭምር ነው።

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo