ፋብሪካችን ሞሓ የለስላሳ መጠጦች ኢንዳስትሪ አክስዩን ማህበር መቐለ ፋብሪካ ፔፕሲ ኮላ ፋብሪካ በተለያዩ የወኪሎቹ የኣይሱዙ ተሽከርካሪዎች 170cm *450cm *220 cm መጠን ያለዉ ሼድ በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት በትግራይ ክልል ፖሊስ ኮምሽን በኮንክሬት ማስተካል ይፍልጋል ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለፁትን የጨረታ መመርያ እማልታቹ መወዳደር ትችላላቹ

ፋብሪካ ልስሉስ መስተ ሞሃ

1 ተጫራቾች በዘርፉ የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ : የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፊኬት: ቫት ተመዝጋቢ መሆኑ የሚያረጋግጥ ሰርተፊኬት እና ቲን ምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

2 ተጫራቾች ለጨረታዉ ማስከበሪያ በኢ/ያ ብሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸዉ እና ሚታወቁ ባንኮች የሚሰጥ በሁኔታ ያለተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም የገንዘብ ክፍያ ማዘዣ ስፒኦ የጠቅላ የጨረታ ዋጋዉ ብር 2% ማስያዝ ይኖርባቸዋል ።

3 የጨረታዉ ዝርዝር ሰነድ ከድርጅቱ ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 12 ድረስ በመምጣት እና ብር 50.00 በመክፈል ሰነዱን መውሰድ ይቻላል።

4 ተጫራቾች አሸናፊ ከሆኑ ስራዉ ለመስራት ዉል ካታሰረበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 3 ሳምንት ዉስጥ ስራዉን ሙሉ በሙሉ አጠናቅቀዉ የማስረከብ ግዴታ ይኖራቸዋል

5 ተጫረቾች ዋጋቸዉ በታሸገ ኢንቨሎፕ ይህን ጨረታ ከወጣበት ግዜ ጀምሮ ከ 04/10/2012ዓ/ም እስከ 11/10/2012 ዓ/ም 8፡15 ሰዓት በስራ ቀንና ሰዓት ኣክሱም ሆቴል ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ዋና ቢሮኣችን ድረስ በመምጣት ለዚሁ ተብሎ በተዘገጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል። በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ እና የሰነዱ ማሽግያ ፖስታ ተጫራቾች ህጋዊ ማህተምና እና ፊርማ መኖር ይኖርበታል።

6 የጨረታ ሳጥኑ 17/10/2012 ዓ/ም ከቀኑ 8:15 የሚታሸግ ሲሆን ከዚሁ ሰዓት ባኃላ የጨረታ ሰነድ የሚመጣ ተቀባይነት ኣይኖረዉም።

7 ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት/ ባልተገኙበትም 17/10/2012 ዓ/ም ከቀኑ ልክ 8:30 በፋብሪካዉ የግዥና ክምችት መምሪያ ቢሮ ወስጥ ይከፈታል።

8 ተጫራቾች በዚህ ጨረታ ላይ ያሸነፋቸዉ የእቃ ዓይነቶች ማሸነፋቸዉ እንደተነገራቸዉ በ7ቀናት ወስጥ የማስረከብ ግዴታ ይኖርባቸዋል።ይህ ሳይሆን ሲቀር ግን ያስያዘዉ የዉል የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ካለ ምንም ቅድመ ሆኔታ ለድርጅቱ ገቢ ይሆናል።

9 ማንኛዉም ተጫራች ጨረታዉ ከተከፈተ ባኃላ ጨረታዉን መሰረዝ ኣይችልም።

10ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በማንኛዉም ግዜ ጨረታዉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።

ለበለጠ መረጃ 03 42 41 52 14 /03 42 41 50 70

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo