1 የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ትግራይ ክልል በራያ አዘቦ ወረዳ ካራ ኣዲሾ ቀበሌ የመንገድ ዳር የገበያ ማዕከል /roadside market shade/ ግንባታ ስራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል

ኤጀንሲ ትራንፎርሜሽን ሕርሻ ኢትዮጵያ ጨንፈር ትግራይ ፅሕፈት ቤት

2 በጨረታዉ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል

3 ተጨራቾች በጨረታ ለመወዳደር በዚሁ የሥራ ዘርፍ የተሰማሩ ሆኖ ህጋዊ የንግድ ፍቃድና የዘመኑን የግብር የከፈሉ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ

4 የግንባታ ሥራ ብቃት የሚያረጋግጥ ከደረጃ 6 እና ከዚ በላይ ማቅረብ የሚችሉ

5 በግንባታ ዘርፍ ስራ ላይ ቢያንስ ሶስት የግንባታ ስራዎችን በኣመርቂ ሁኔታ ያስረከበ ለዚሁም ማረጋገጫ ማያያዝ ይኖርባቸዋል

6 የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ

7 የኣቅራቢነት ምዝግባ ምስክር ወረቀት ወይም በግዥ ኤጀንሲ ዌብ ሳይት ላይ የተመዘገቡ

8 የግብር ግዴታቸዉን ሰለመወጣታቸዉ የሚያሳይ ማረጋገጫ የሚቀርቡ

10 ተወዳዳሪዎች ሰነዳቸዉን ሲያቀርቡ የፋይናንስና የቴክኒክ ሰነዶችን ላይተዉ በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

11 ተወዳዳሪዎች ለስራዉ የሚያቀርቡት ዋጋ መሥራያ ቤቱ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ባቀረበዉ የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ የተሞላ ዋጋ መቅረብ አለበት

12 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 በባንከ በተረጋገጠ ማስያዝ አለባቸዉ የባንክ ዋስትና የሚያስዙ ከሆነ በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ለ118 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸወዋል የኢንሹራንሱ ሰነድ ተቀባይነት የለዉም

13 ጨረታዉ መጋቢት 23ቀን 2012 ዓም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ላይ የተጫራቾች የቴክኒካል እና የዋጋ ማወዳደሪያ ሰነድ በተመሳሳይ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ትገራይ ቅጽቤት የመሰብሰቢያ ኣደራሽ በይፋ ይከፈታል

14 በኣማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀዉን የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 200 በመክል ከግብርና ትራስፎርሜሽን ኤጀንሲ ዋናዉ መስሪያ ቤት ወይም መቀሌ ከሚገኘዉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መዉሰድ ይችላሉ

15 ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ላይ ማብራረያ ቢፈልጉ ከዚህ በታች በተገለፀዉ ኣድራሻ መጠየቅ ይቻላሉ

16 መስሪያ ቤቱ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልመ ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

ስልክ 251 115 570665/ +251 342 405397/0911 660518

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo