ለ 2ተኛ ግዜ የወጣ ግልፅ የጨረታ ማስታወቅያ የኢትዮጵያ መንገድ ፈንድ በትግራይ ክልል ለሚገኙ የገጠርና ከተማ የመንገድ ኤጀንሲዎች ለመንገድ ጥገና የ2012 ዓመት በጀት የመደበ ሲሆን ከዚሁ ከተመደበው በጀት ውስጥ ለመንገድ ኤጀንሲዎች የሚሠት የመንገድ ጥገና ሥራ የኮንሰልታንሲ ሰርቪስ ግልፅ ጨረታ አጫርቶ ለኢትዮጵያ መንገድ ፈንድ እንዲያቀርቡ የትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መንገድ ልማትና አስተዳደር ከኢትዮጵያ መንገድ ፈንድ ፅ/ቤት በተሰጠው ሙሉ ውክልና መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት ማሟላት የሚችሉ ሁሉ በግልፅ ጨረታው መሳተፍ ይችላል፡፡

ብሄራዊ ክልላዊ መንግስቲ ትግራይ ቢሮ ኮንስትራክሽን መንገድን ትራንስፖርትን

1/የ2012 ዓ.ም የአማካሪነት ንግድ ሥራፍቃድ ተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያለፈው ወር ዲክላሬሽን የግብር ክፍያ መለያ ቁጥር /TinNo/የታደሰ የአቅራቢዎች ምስክር ወረቀት ፈቃድ ያላቸው ሕጋዊ አማካሪዎች በተጨማሪ ከኮንስትራክሽን ሚኒስተር ወይም ውክልና ከተሰጠው አካል የ2012 ዓ.ም የታደሰ የአማካሪነት ፈቃድ ማቅረብ የሚችል፡፡

2/በመንገድ ፈንድ ሙሉ ውክልና የተሰጠው የትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ዳይሬክቶሬት የመንገድ ልማትና አስተዳደር በ (Highway and bridge consultancy and construction management consultancy) ደረጃ -3 እና ከዚህ በላይ አማካሪዎች፡፡

3/ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፈቀደላቸው ከታወቁ ባንክ በሚሰጥ የተረጋገጠ ያለገደብ (Unconditionalbankguarantee) ሲፒኦ ወይም በካሽ ብር 20,000.00 ብር /ሃያ ሺህ ብር / ለቢሮ ኮንስትራክሽን መንገድ ትራንስፖርት ማቅረብ ይገባቸዋል፡፡

4/ ተጫራቾች ለተጫረቱበት Consultancy Service for the Supervision and Contract Administration of Road Maintenance Program for Tigray region Urban and Agencies የሥራ ውል ከተፈጸረመበት ቀን ጀምሮ በትንሹ ለአሥራ ሁለት ተከታታይ ወራት /365 ቀናት/ ሙሉ በሙሉ ሥራውን መስራት አለበት፡፡

5/ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከ13/06/2012 ዓ.ም ጀምሮ ከትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ዳይሬክቶሬት የመንገድ ልማትና አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 152 አስፈላጊውን ማስረጃ በማስያዝ የማይመለስ ብር 300.00/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።

6/ተጫራቾች የሚጫረቱበት የኮንሰልታንሲ ሰርቪስ ዋጋ ፋይናንሻል/ እና ቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦርጅናል ሁለት ፎቶ ኮፒ እያንዳንዳቸው በተለያዩ ፖስታዎች ታሽገው የ2012 ዓ.ም የታደሰ የአማካሪነት ንግድ ስራ ፍቃድ የባለፈው ወር ዲክላሬሽን የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TineNo/ የአቅራቢዎች ምስክር ወረቀት ፈቃድ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለያንዳንዳቸው በፖስታ በማሸግ እንዲሁም ሁሉንም ጠቅልሎ በሚይዝ ትልቅ ፖስታ ላይ በሚታይ ፅሁፍ ተፅፎ በትግራይ ክልል ኮንስትራክሽን መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ በዳይሬክቶሬትመንገድልማትና አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 152 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ ቀን /እስከ 20/06/2012 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርበታል፡፡

7/ጨረታው የሚዘጋበት ቀን በ20/06/2012 ዓ.ም በ4፡00 ሰዓት ከሰዓት በፊት ሆኖ በተመሳሳይ ቀን 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 152 በጨረታ ኮሚቴ ፊት ይከፈታል።

8/ተጫራቾች ወደ ዋጋ/financial/ መወዳደሪያ ሰነድ ለመግባት ዝቅተኛው የቴክኒካል ነጥብ 70%/ሰባ ፐርሰንት /ማግኘት አለባቸው የቴክኒካል ዝቅተኛ ነጥብ ያላገኙ ተጫራቾች የዋጋ መወዳደሪያ ሰነዳቸው ሳይከፈት ይመለሰላቸዋል፡፡

9/ቢሮው የተሻለ አማራጭ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሠረዝ መብት የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ ለዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መንገድ ልማትና አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 210 ሦስተኛ ፎቅ ወይም

አድራሻ ስልክ ቁጥር፡- 0344-41-06-45/0344-40-00-50

ፓ.ሳ.ቁ 225

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo