ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም አ/ማ ለድርጅቱ አገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ መኪኖች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ደደቢት ትካል ልቓሕነ ምዕቓሪን/ደደቢት ትፍልም/

1 የ2012 ዓም ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ምስክር ወረቀት የንግድ ምዝገባ ሰርተፊኬት የተመዝገባችሁ መሆኑን የሚገልፅ እና የባለፈዉ ወር ቫት ዲክለሬሽን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

2 ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን CPO ወይ Unconditional Bank Guarantee 200,000.00 / ሁለት ሞቶ ሺ ብር /ማስያዝ አለባቸዉ

3 ሁሉም ተጫራቾች ጨረታ ሰነድ 28/ 05/2012 ዓም ጀምሮ እስክ 06/06 /2012 ዓም በኣዲስ አበባ ተክለሃይማኖት ቅርንጫፍና መቐለ በሚገኘዉ ዋና መስሪያ ቤታችን ደደቢር ብድርና ቁጠባ አ/ማ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 409 አስፈላጊዉን ማስረጃ በመያዝ የማይመለስ ብር 150 በመክፈል ዝርዝር የጨረታ ሰነድ መዉሰድ ይችላሉ

4 ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ዉስጥ ያሉ ቅፆችን በትክክል በመሙላት በየኣንዳንዱ ገፅ በመፈረም እና ማህተም በማድረግ ምንም ገፅ ሳያጎድሉ ማቅረብ አለባችሁ የጎደለ ገፅ ወይም የተዛባ ሰነድ ማቅረብ ከጨረታ ዉጭ ያደርጋል

5 ተጫራቾች የተጫረቱበትን ጀነሬተሮች ቴክኒካል ፋይናንሻል ኣንድ ኦርጅናል ኣንድ ኮፒ እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያ ሰነድ በተለያዩ ፖስታዎችን በማሸግ ሁሉንም ፖስታ በትልቅ ፖስታ በማሸግ መቐለ ዋና ቢሮ በ4ኛ ፎቅ በተዘጋጀዉ ሳጥን ገቢ ማድረግ ይኖርበቸዋል

6 ጨረታዉ 06/06/2012 ዓም ከጥዋቱ 3:00 ተዘግቶ በድርጅታችን የቀረበዉን ሰነድ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኹበት እንዲሁም የተማላ ደኩሜንት ከሆነ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ባይኖሩም ከጥዋቱ 3:30 ይከፈታል

7 የጨረታዉ አሸናፊ ዉጤት እንደተገለፀ በኣምስት ቀን ዉስጥ ዉል ማሰር ይኖርበታል

8 የጨረታዉ አሸናፊ የጨረታዉ ዉጤት እንደተገለፀ የመልካም ስራ አፈፃፀም ከጠቅላላ ዋጋ 10 % CPO ወይ Unconditional Bank Guarantee ማስያዝ ይኖርበታል

9 ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት በ90ተከታታይ ቀናቶች ዉስጥ ሙሉ በሙሉ ኣምጥቶ ገጥሞ ማስረከብ የሚችል

10 ድርጅቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

11 ለበለጠ መረጃ ዋና ቢሮ ሶስተኛ ፎቅ ቁጥር 11 ወይም በስልክ ቁጥር 0342 400014 መቐለ ዋና ቢሮ በመደወል ማረጋገጥ የምትችሉ መሆናችሁን እንገልፃለን

ስፖንስርታትና

The ways ideas spread.
Milkta Logo