ራያ ዩኒቨርሲቲ ከላይ በሰንጠረዡ የተመለከተውን ምድቦች በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ዕቃዎች ወይም አገልግሎት መግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው።

ራያ ዩኒቨርስቲ

ጨረታ ዝወፀሉ ዕለት 4/ 13 /2010 ዓም ምድብ 

1 የመኪና ሰረቪስ ማድረጊያ ጋራጅ, ሰፒኦ: 30,000.00 

ምድብ2 የዳቦ አቅርቦት ግዥ , ሰፒኦ :25,000.00 

ምድብ 4 የአትክልት አቅርቦት ግዥ ለ2ኛ ጊዜ የወጣ, ሰፒኦ: 15,000.00 

ምድብ 5 የጽህፈት መሳሪያ ዕቃዎች ግዥ ,ሰፒኦ: 30,000.00 ምድብ 6 የኩሽና ዕቃዎች አቅርቦት ግዥ, ሰፒኦ: 30,000.00 

1. ተጫራቾች የ2010/2011 ዓ.ም ሕጋዊ ለየምድቡ በዘርፉ የታደሰ ፍቃድ፣ የዘመኑን ግብር መከፈላቸውን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢው ባለሥልጣን ጊዜው ያላለፈበት የንግድ የተሰጠ የምስክር ወረቀት ወይም ታክስ ክሊራንስ፣ የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት፣ በፌዴራል የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የአቅራቢዎች ዝርዝር ወይም ሳፕላይ ሊስት ውስጥ በዌብሳይታቸው በዕቃ/በአገልግሎት አቅራቢነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።

2. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) ብቻ በመክፈል ጨረታው በጋዜጣ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 16 ቀናት በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ አድሚን ሕንፃ ቁጥር 5 ግዥ ቡድን 2ኛ ፎቅ ዘወትር በሥራ ሰዓት በመቅረብ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።

3. ተጫራቾች የቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዳቸውን አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ ለምድብ አንድ፣ ሁለትና አምስት ብቻ በተለያየ ፖስታ በማሽግ የጨረታ ሳጥኑ ከመዘጋቱ በፊት ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት በ16ኛው ቀን እስከ ጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከላይ በተራ ቁጥር 2 በተመለከተው አድራሻ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

4. ጨረታው በ16ኛው ቀን ልክ 3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ውስጥ በግዥና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት አድሚን ሕንፃ ቁጥር 5 ግዥ ቡድን 2ኛ ፎቅ ይከፈታል። ነገር ግን 16ኛው ቀን ሃይማኖታዊ ወይም መንግሥታዊ በዓል ከሆነ በቀጣይ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ የሚከፈት ይሆናል።

5. ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ይህ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ60 ቀናት ይሆናል።

6. የጨረታ ማስከበሪያ ከታወቀ ባንክ በሚሰጥ የክፍያ ማዘዣ ቼክ ወይም የባንክ ዋስትና ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሌተርኦፍ ክሬዲት በፖስታ ታሽጎ ለብቻው ማህተምና ፊርማ ተደርጎ መቅረብ ይኖርበታል።

7. አሸናፊ ተጫራች ዕቃዎችን ከምድብ አንድ ውጪ በራሱ ትራንስፖርት እስከ ራያ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የማቅረብ ግዴታ አለበት።

8. ዩኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

9. ለበለጠ መረጃ፡- www.rayu.edu.et ወይም በስልክ ቁጥር:- 03-48-77-0501/03-48-77-05-46 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo