የፕሮፎርማ ማስታወቅያ (Shopping)
የመቐለ እቅድና ፋይናንሰ ፅፈት ቤት በከተማችን በልማታዊ ሴፍትኔት ባጀት በመጠቀም ለሚሰሩ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የሚዉል የተለያዩ የሼድ (SMALL METAL SHADES FOR EY HOOD_BENEFICIARIES) በሾፒንግ ፕራፎር ኣወዳደሮ ለማሰራት ስለሚፈልግ በዚ ጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉና ከታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች የምታማሉ ህጋዊ ተጫራቶች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
CONTRACT /BID/NO ET-TIGRAY-MEKELLE-432017-CW-RFQ
ተፈላጊ መስፈርቶች
1/ ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ጨረታዉ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 300.00 ብር በመክፈል ከመቐለ እቅድና ፋይናንሰ ፅ/ፈት ኣግኣዚ ኦፕሬሽን ህንፃ በሚገኝዉ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 034 መግዛት ይችላሉ።
2/ የዘመኑ የታደሰ ንግድ ስራ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ፣ የኣቅራቢነት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ፣ የቫት ምዝገባ ሰርቲፊኬት ' የቅርብ ወር ቫት ሪፖርት ፣ ብቃት መረጋገጫ ሴርቲፍኬት ማቅረብ የሚችሉእና የግንባታ ሰራ ዘርፍ የተሰማሩ መሆን ኣለባቸዉ።
3/ የመወዳደሪያ ሀሳቡ ከ 08/08/2017 ዓ/ም እስከ16/08/2017 ዓ/ም ሰአት4:00 ለተጫራቾች ክፍት ሁኖ የሚቆይ ሲሆን በዚህ ቀን 4:00 ተዘግቶ 4:30 ሰዓት ቢሮ ቁጥር 034 ይከፈታል፡፡
4/ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ብር 150,000 (ኣንድ መቶ ሃምሳ ሺ ብር ብቻ ) በCPO ፣ ወይም በጥሬ ገንዘብ ወይም የባንክ ዋስትና(Unconditional ) ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ኣለባቸው :: የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታው ከተከፈተበት ግዜ አንስቶ ለ33ቀናት ይሆናል ፡፡
5/ የግንባታ ስራ የሚጀመረዉ ትዕዛዝ ከተሰጠበተ ቀን ጀምሮ 45 ተከታታይ ቀናት ይሆናል፡፡
6/ በግንባታ ስራዉ ጠቅላላ ዋጋውን በቁጥር መፀሃፍ ኣለባቸው ፡፡ የነጠላ ዋጋ (ዩኒትፕራስ) ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ መካከል ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡
7/ ተጫራቾች የሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ፊርማቸው ፣ ቀን እና የድርጅታቸው ማህተም ማስፈር ይገባቸዋል ፡፡
8/ በጨረታዉ መሳተፈ የሚችሉት በግንባታ ስራዉ ቢያንስ ኣንድ እና ከዚያ በላይ ተመሳሳይ ስራ የሰሩ መሆን ኣለባቸዉ፡፡
9/ የክፍያ ሁኔታ በየግንባታዉ ደረጃ እየታየ የሚከፈልበት ሁኔታ ለተጠናቀቀዉ ስራ በባለሙያ በሃላፊ እየተረጋገጠ መክፈል እንዳለበት በስምምነት ላይ ሊደርስ ይችላል፡፡
10/ የመወዳደርያ ሀሳብ ማቅረብያ ቛንቛው ኣማርኛ ነው ፡፡
11/ በግንባታ (ኣገልግሎት) ስራዉ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች (BOO) ተያይዟል ፡፡
12/ ማንኛውም ተጫራችች ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰአት በፊት የዋጋ ማቅረቢያው ሰነዱን /የመወዳደርያ ሀሳብ / ማስገባት ይኖርበታል ፡፡ ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰአት በኋላ የቀረበ የዋጋ ማቅረብያ ሰነድ /የመወዳደርያ ሀሳብ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን ኢንቨሎፑ ሳይክፈት ለተጫራቹ ተመላሽ እንዲሆን ይደረጋል፡፡
13/ መስራቤቱ የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታዉ (ሾፒንግን) በከፊል(በሙሉ) የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
14/ የመወዳደርያ ሂሳቡ ዋጋ የሚቀርበው በኢትዮጵያ ብር ነው ''
15/ የጨረታ መወዳደሪያው በሚከተለው መሰረት ይሆናል ፡
15.1/በግንባታ ስራዉ ቴክኒካል መስፈርቶቹን ያማሉ መሆናቸው ይረጋገጣል፡፡
15.2/በቀረበው ዋጋ ላይ የሂሳብ ድምር ስህተት ካለ እንዲታረም ይደረጋል ፡፡
15.3/ውድድሩ የሚካሄደውእና ዝቅተኛ ዋጋ ኣቅራቢ የሚለየው በታረመው ዋጋ መሰረት ይሆናል ፡፡
16/ ጨረታው ህጋዊ መስፈርቱን ካማለት ኣቅራቢዎች መካከል ዝቅተኛ ዋጋ ላቀረበው ተጫራች ኣሸናፊ ይደረጋል ::