አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ ቁጥር FIS/01/2016 መሠረት የውጭ አገር ዜግነት ከያዙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ባለአክስዮኖች ቀደም ሲል ከተረከባቸው ውስጥ ብር 29,125.00 ዋጋ ያላቸው 1165 ተራፊ አክስዮኖችን ኢትዮጵያዊ ለሆኑ ዜጎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሽጥ ይፈልጋል

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ ቁጥር FIS/01/2016 መሠረት የውጭ አገር ዜግነት ከያዙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ባለአክስዮኖች ቀደም ሲል ከተረከባቸው ውስጥ ብር 29,125.00 ዋጋ ያላቸው 1165 ተራፊ አክስዮኖችን ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሠረት ኢትዮዽያዊ ለሆኑ ዜጎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሽጥ ይፈልጋል።

ስለሆነም በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ሐምሌ 19 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን በማቅረብ መጫረት ይችላሉ                               

ተጫራቾች ሊያሞላቸዉ የሚገቡ መስፈርቶች


  1. ኢትዮዽያዊ ዜጋ የሆኑ ተጫራቾች መጫረት የሚፈልጉትን አክሲዮኞች መጠን ለዋጋ ማቅረቢያ የተዘጋጀውን ቅጽ ከባንኩ ዋና መ/ቤት የአክስዮን አስተዳደር ክፍል ወስደው በመሙላት፣ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚጫረቱበትን የአክስዮኖች ጥቅል ዋጋ 1/4ኛ በባንኩ በተረጋገጠ ሲፒኦ እንዲሁም ተጫራቾች ኢትዮዽያዊ ዜጋ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ፤ ወይም ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ ኮፒ አያይዘው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ሃያ ሁለት አካባቢ 'ሌክስ ፕላዛ 4ኛ ፎቅ በሚገኘው የባንኩ ዋና መ/ቤት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እስከ ነሐሴ 4 ቀን 2012 . ከቀኑ 1000 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  2. ጨረታው ነሐሴ 5 ቀን 2012 . በባንኩ ዋና /ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 400 ሰዓት ላይ ይከፈታል።
  3.  የጨረታው አሸናፊዎች ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ አሽናፊ መሆናቸው ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ በአምስት የስራ ቀናት ውስጥ ለባንኩ ገቢ በማድረግ አስፈላጊውን ፎርማሊቲ ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
  4. በጨረታው ተሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ውጤቱ እንደታወቀ ለባንኩ ያስያዙት የጨረታ ዋስትና ወዲያውኑ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
  5.  በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያዎችና በሌሎች የተደነገጉ ተያያዥ ሕጎች ተፈፃሚነት አላቸው::

ባንኩ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo