ሰላም የህዝብ ማመላለሻ አ/ማህበር ሲገለገልባቸው የነበሩ አውቶብሶችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል

ሰላም የህዝብ መጓጓዣ ኣ/ማ
  1. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የተሽከርካሪዎቹን ዝርዝር የያዘውን የመወዳደሪያ ሰነድ ከዋናው መ/ቤት መስቀል አደባባይ ፊንፊኔ ህንጻ ፋይናንስ መምሪያ 5ተኛ ፎቅ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ በመክፈል መውሰድ ይችላል።
  2. ተጫራቾች ለጨረታው ማስከበሪያ የጨረታ ዋጋው 20% (ሃያ በመቶ) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  3. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የመወዳደሪያ ዋጋ በሰም በታሸገ ፖስታ በማዘጋጀት ማስታወቂያው ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ሰኔ 15 ቀን 2012 ዓ/ም መግዛት ይችላሉ፡፡
  4. ጨረታው ሰኔ 16 ቀን 2012 ዓ/ም 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ3፡30 ሰዓት በአ/ማህበሩ ዋና መስሪያ ቤት 4ተኛ ፎቅ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  5. የጨረታው አሸናፊ ማሸነፉ በደብዳቤ ከተገለጸለት ዕለት ጀምሮ በ10 ቀናት ውስጥ ገንዘቡን ከፍሎ ተሽከርካሪውን ማንሳት አለበት፡፡ በተጠቀሰው ቀን ውስጥ ካላነሱ የጨረታው አሸናፊ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ ለአ/ማህበሩ ገቢ ሆኖ ንብረቱ ለ2ተኛ አሸናፊ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
  6. የተሽከርካሪውን የስም ዝውውርና ህግ የሚጠይቃቸውን ማንኛውም ክፍያዎች (ወጪዎች) አሸናፊ የሚሸፍን ይሆናል።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከገዙበት ዕለት ጀምሮ ዮሴፍ ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው የአ/ማህበሩ ጋራዥ በመገኘት አውቶቢሶቹን በስራ ሰዓት ማየት ይችላሉ።
  8. ተጫራቾች የሚያቀርቡት የመጫራቻ ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆኑን መግለጽ ይኖርባቸዋል።
  9. አ/ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ ማብራሪያ

በስልክ ቁጥር 09-14-70-38-08 ወይም 011 4 70 83 32 ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ፤

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo