የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት ለፕሮጀክቱ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ጀኔሬተሮች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ስለሚፈልግ በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ እና የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል፡፡

የወልቃይት ስኮር ልማት ፕሮጀክት
  • ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን :  14/4/2012
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን : በ16ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 3:00
    ጨረታዉ የመከፈትበት ቀን : በ16ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 3:30
  • የዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት (TIN no.) እና በመንግስት የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ምስክር ወረቀት ኮፒ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  • ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸው የማያረጋግጥ ምስክር ወረቀትና የጥቅምት ወር 2012 ዓ/ም ቫት ዲክላሬሽን ኮፒ ማቅረብ አለባቸው::
  • ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም ጥሬ ገንዘብ ወይም የባንክ ዋስትና ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ወይም ከጨረታ ሰነድ ጋር በወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት ስም ማቅረብ አለባቸው::
  • ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር ሰነድ የማይመለስ ብር 50 በመክፈል በመቀሌ ከተማ የትግራይ ልማት ማህበር 2ኛፎቅ ቢሮ ቁጥር 375 ከሚገኘው የፕሮጀክቱ ማስተባበርያ ፅ/ቤት | ላይዘን ኦፊስ ወይም ከወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት አቅርቦትና ፋሲሊቲ መምሪያ በግዥ ቡዱን ቢሮ ቁጥር 1 የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች የሚጫረቱበት ዋጋ በግልፅ በታሸገ ኢንቨሎፕ በመቀሌ | ከተማ የትግራይ ልማት ማህበር 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 375 ከሚገኘ የፕሮጀክቱ ማስተባበርያ ፅ/ቤት / ላይዘን ኦፊስ | ለዚህ ጨረታበተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች ይህ ማስታወቅያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት በ16ኛው ቀን ከጧቱ 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚህ ቀን ጧት 3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመቀሌ ከተማ የትግራይ ልማት ማህበር ሰሚገኘው የፕሮጀክቱ ማስተባበሪያ ጽ/ ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 375 ይከፈታል 

ፕሮጀክቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- ለወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት /0914001262/091052095/09 29184332 

 ለመቀሌ ላይዘን ኦፊስ 0344416452 | 0914780795 በመደወልመጠየቅ ይቻላል 

የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo