በትግራይ ክልል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ኮንስትራክሽን ማሽነሪ ኢኩፕመንት ለ2012 በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ
  1. ተጫራቾች የዘመኑ የ2011/12 ግብር የከፈሉና ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ መሆን አለባቸው።
  2. ተጫራች ቫት የተመዘገበበት ቲን ሰርተፍኬትና ፣ በአቅራቢነት የተመዘገቡበት ማስረጃ፣ ጥቅምት/ ሕዳር 2012 ዓ/ም ቫት የከፈለበት /ዲክለሬሽን/ ማቅረብ አለበት።
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ- ሎት-1 ኮንስትራክሽን ማሽነሪ ኢኩፕመንት ብር 150,000.00/ አንድ መቶ ሃምሳ ሺ ብር)፣ በጥሬ ገንዘብ ወይም በተረጋገጠ ቼክ ወይም CPO፣ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው ከታወቁ ባንኮች የተሰጠ በማንኛውም ሁኔታ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ ከታወቀ ባንክ ከጨረታው መከፈቱ በፊት ማቅረብ ማስያዝ/ አለባቸው
  4. አሸናፊዎች የሆናችሁ ተወዳዳሪዎች በ30 ተከታታይ ቀን ውስጥ ወደ ቦታው ማድረስ አለባችሁ
  5. የተዘጋጀው የተጫራቾች መመሪያና ዝርዝር ሰነድ ጨረታ ዶክመንት የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ከቢሮ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ትግራይ ክልል የግዢ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 333 በመቅረብ በገዛችሁት ሰነድ ዝርዝር ዋጋ በመሙላት በታሸገ ፖስታ አንድ ኦርጂናል ዋጋ የተሞላበት በማዘጋጀት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ከ10/4/2012 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 27/4/2012 ዓም በአካል በመቅረብ ለጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን በማስገባት መወዳደር ይቻላል።
  6. ጨረታ ሳጥን የሚዘጋበት ቀን 27/4/2012 .ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 27/4/2012 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ዓት ከሰዓት በኋላ ተጫራች ወይም ሕጋዊ ወኪል በተገኘበት ቢሮ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ትግራይ ክልል ይከፈታል።
  7.  እቃዎቹ የሚደርሱበት ቦታዎች ዝርዝር ኮሌጆች በተጫራቾች መምሪያ ማየት ይቻላል
  8. ቢሮ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻችን፡-

  • መቐለ ዓዲ ሓቂ ኮምብሌክስ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 333 ፊት ለፊት በደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ በስራ ሰዓት በስልክ ቁጥር፡- 0344403447ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

በትግራይ ክልል የቴክኒክና ሙያ

ትምህርትና ስልጠና ግዥ ፋይናንስ ንብረት

አስተዳደር ዳይሬክቶሬት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo