በኢፌዲሪ በግል ድርጅቶች ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ሰሜን ሪጅን ፅ/ቤት አላቂ እና ልዩልዩ የፅህፈት መሳርያዎች፣ኣላቂ የፅዳት ዕቃዎች፣ ለሠራተኞች ቆዳ ጫማ ፣ ለደንብ ልብስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

በኢፌዲሪ በግል ድርጅቶች ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ሰሜነ ሪጅን ፅ/ቤት
  • 1ኛ ሎት አላቂ እና ልዩልዩ የፅህፈት መሳርያዎች፣
  • 2ኛ ሎት ኣላቂ የፅዳት ዕቃዎች፣
  • 3ኛ ሎት ለሠራተኞች ቆዳ ጫማ ፣
  • 4ኛ ሎት ለደንብ ልብስ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች
  1. የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸውና የእቃ ኣቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  2. የግብር መክፈያ መለያ ቁጥር ቲን ነምበር ና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣
  3. የጨረታ ማስከበርያ (CPO) ፣
  • 1ኛ ሎት ለአላቂ እና ልዩልዩ የፅህፈት መሳርያዎች ብር 1,500.00
  • 2ኛ ሎት አላቂ የፅዳት ዕቃዎች ብር 1,000.00
  • 3ኛ ሎት ለሠራተኞች ቆዳ ጫማ ብር 1,500.00
  • 4ኛ ሎት ለደንብ ልብስ ብር 1,500.00

ሲሆን በጥሬ ገንዘብ ወይም ሰርቲፋይድ ቼክ (CPO) ማስያዝ የምትችሉ ተጫራቾች የተዘጋጀዉን የጨረታ ሰነድ 

የማይመለሰ ብር 30 (ሠላሳ ብር ብቻ) መክፈል ከሪጅን ፅህፈት ቤቱ ከታህሳስ 08 2012 ዓ/ም ጀምሮ  ሰነዶችን  በመግዛት ለተከታታይ 15 ቀናት እስከ ታህሳስ 23 2012 ዓ/ም ባሉት ቀናት  ውስጥ በስም  በታሸገ ኢንቨሎፕ  በማድረግ  በሪጅን ፅ/ቤቱ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ሊያስገቡ ይችላሉ::

4.  ጨረታዉ ታህሳስ 23 2012 ዓ/ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሽጎ በእለቱ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች  ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በሪጅን ፅ/ቤቱ አዳራሽ ይከፈታል ፤ የተጠቀሰው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ የስራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት ይሆናል ፣

5. ተጫራቾች ቢሮው ባወጣው ሰነድ ላይ ዋጋቸውን መሙላት ኣለባቸው ፣

6, ሪጅን ፅ/ቤቱ የተሻለ የአሰራር ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል  የመሰረዝ  መብቱ የተጠበቀ ነው ፣

አድራሻችን፡ መቐለ ቀበሌ 11 ታሀገዘ ህንፃ ግራውንድ ላይ እንገኛለን::

ለበለጠ መረጃ፣ በስልክ ቁጥር 0342-40-54-43 እና 0344-40-12-90 መጠየቅ ይቻላል::

የኢፌዲሪ የግል ድርጅቶች ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጄንሲ

ሰሜን ሪጅን ፅ/ቤት መቐለ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo