በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅ/ጽ/ቤት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የመኪና ኪራይ አገልግሎት ግዥ አገልግሎት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን

ድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ 

የግዥ መለያ ቁጥር: ERCCMB/NCB004/2012 

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅ/ጽ/ቤት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የሚከተለውን አገልግሎት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል። 

  • ሎት አንድ፣ የመኪና ኪራይ አገልግሎት ግዥ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል። 
  1.  ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና ቲን ሰርተፊኬት ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ 
  2. በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚ/ ር አቅራቢነት ፍቃድ ወይም በክልል እቅድና ፋይናንስ ቢሮ የተሰጠ የአቅራቢነት ፈቃድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል። 
  3. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ ። 
  4. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል። 
  5. የጨረታ ማስከበርያ ብር 10,000.00/አስር ሺህ /በባንክ በተመሠከረለት ቼክ ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ወይም ጥሬ ገንዘብ ከጨረታው መክፈቻ በፊት ማቅረብ ይኖርባችኋል።
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ኢ/ያ አጠገብ የሚገኘው የውሃንስ ግደይ ህንፃ ላይ ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 1 ማስገባት ይችላሉ። 
  7. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ታህሳስ 11 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4:30 በመስሪያ ቤቱ ሁለተኛ ፎቅ ሃብት አስተዳደር ቢሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 
  8. የጨረታው አሸናፊ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) CPO ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል። 
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

ስልክ ቁጥር 03424071162/0919068385/0914830469 

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቐለ ቅ/ፅ/ቤት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo