በሃገር መከላኪያ ሚነስቴር የሰሜን ዕዝ ጠቅላላ መምሪያ ለ2008 ዓም በጀት ዓመት አገልግሎት የሚዉሉ ከዚህ በታች የተገለፁትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

መከላለያ ሰሜን ዕዝ ጠ/መምርያ

1 ሎት 1 ኣላቂ የጽህፈት መሣሪያ

2 ሎት 2 የጽዳት እቃዎች

3 ሎት 3 የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች እና የኦፊስ ማሽን መለዋወጫ ዕቃዎች

4 ሎት 4 መጋረጃ እና የወለል ምንጣፍ

5 ሎት 5 የኮንስትራክሽን ዕቃዎች

6 ሎት 6 የአዳራሽ ወንበር

7 ሎት 7 የጀነሬተር መለዋወጫ እና የኮምፒተር መለዋወጫ ዕቃዎች

8 ሎት 8  የኤሌክትሪክ ዕቃዎች

9 ሎት 9 ብሎኬት ጠጠር ድንጋይ እና አሸዋ

10 ሎት 10 አጠናዎች

11 ሎት 11 የተለያዩ አልባሳት እና የቆዳ ዉጤቶች

በሥራዉ የተሰሩ ህገዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸዉና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸዉን ማቅረብ የሚችሉ ለሚቀርቧዉ ዕቃዎች ኦርጅናል ለመሆናቸዉ ማስረጃ መስጠት የሚችሉ አቅራቢዎችን ይጋብዛል

ተጫራቾች የጨረታዉን ዝርዝር መመርያ እነ ዝርዝር ሰነድ የማይመለስ በተ.ቁ 1: 2 :4: 8 :9 እና 10 ለያንዳንዳቸዉ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር/ በተ.ቁ 3: 5 :6 :7 እና 11 ለእያንዳንቸዉ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት መቀሌ ኩሓ መንገድ እግር ወንበር አካባቢ ከሚገኘዉ የጠቅላላ መምሪያ ግዥ ቡድን ቢሮ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመግዛት በቢሮዉ ወደ ተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እያሰዉቅን ጨረታዉ ታህሳስ 8/2008 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4:15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ  

 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo