የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የላቦራቶሪ ኬሚካልስ፤የላቦራቶሪ መገልገያ እቃዎች (Laboratore Equipment) የአቨካዶ ዘር፤ የቢሮ እቃዎች፤/ፈርኒቸር/ የፅዳት እቃዎች፤ የፅህፈት መሳሪያዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ
  • ሎት 1 የላቦራቶሪ ኬሚካልስ
  • ሎት 2 የላቦራቶሪ መገልገያ እቃዎች (Laboratory Equipment)
  • ሎት 3 የአቨካዶ ዘር
  • ሎት 4 የቢሮ እቃዎች /ፈርኒቸር/
  • ሎት 5 የፅዳት እቃዎች
  • ሎት 6 የፅህፈት መሳሪያዎች 

በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፤ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶክሜንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮኣችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል። 

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የVat ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tin) እና ያለፈው ወር ቫት (Vat) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት፣ 
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው፤
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በ CPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ጨረታው ታህሳስ 14 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የመሰብሰብያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 0344403663/ 0344404346 ወይም በፋክስ ቁጥር 0344409971/ 0344403663 መጠየቅ ይቻላል። 

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo