የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የተለያዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ማለትም፡-የፀረ ተባይ ኬሚካል፣ የጓሮ አትክልት ዘር፣ የእንስሳት መድሃኒት ለ2ኛ ጊዜ የወጣ፣ የእንስሳት መድሃኒትና መገልገያ መሳሪያዎች ለ2ኛ ጊዜ የወጣ፣ ሰው ሰራሽ የእንስሳት ማዳቀያ ማሽን መለዋወጫ እቃዎች ለ2ኛ ጊዜ የወጣ፣ ጄኔሬተር፣ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ
  • ሎት 1 የፀረ ተባይ ኬሚካል፣ 
  • ሎት 2 የጓሮ አትክልት ዘር፣ 
  • ሎት 3 የእንስሳት መድሃኒት ለ2ኛ ጊዜ የወጣ፣ 
  • ሎት 4 የእንስሳት መድሃኒትና መገልገያ መሳሪያዎች ለ2ኛ ጊዜ የወጣ፣ 
  • ሎት 5 ሰው ሰራሽ የእንስሳት ማዳቀያ ማሽን መለዋወጫ እቃዎች ለ2ኛ ጊዜ የወጣ፣ 
  • ሎት 6 ጄኔሬተር፣ 

በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ፤ በመሆኑም በጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶክመንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል እና ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል። 

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርቲፊኬት፣ የVat ሰርቲፊኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና ያለፈው ወር ቫት (Vat ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት፣ ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው፤ 
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በCPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤ 
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፤ 
  • ጨረታው ታህሳስ 13/2012ዓምከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የመሰብሰብያ አዳራሽ ይከፈታል። 
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን መሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0344403663/0344404346 ወይም 
  • ፋክስ ቁጥር 0344409971/0344403663 መጠየቅ ይቻላል። 

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo