የመቐለ ውሃ አገልግለት ጽ/ቤት ለ2012 ዓ/ም በጀት አመት የሚያገለግል ዲ ሲኣይ (ሲአይ )፣ ጂኤስ (ጂኣይ) ትቦ እና መገጣጠሚያዎች ኤች ዲ ፒ መገጣጠሚያ (DCI/CI, GS/GI PIPES & FITTINGS &) HDPE Fittings ግዥ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሳተፍ ለምትፈልጉ ተጫራቶች ጥሪውን ያቀርባል :

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት

ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን ህዳር 7/2012 ዓም

ጨረታዉ የሚዘጋበተ ቀን በ30ኛዉ ቀን 2012 ዓም 4:00 ሰ




ዓት   

ጨረታዉ የሚከፈተበት ቀን በ30ኛዉ ቀን 2012 ዓም 4:30 ሰዓት                                                                                                                                                                              

  1.  


  1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የእቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው፡፡ 
  2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ
  3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ/በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ 
  4. ጨረታ ዶክሜንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 2012 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ፤ 
  5.  ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30ኛው ቀን 2012 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ተጫራች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 
  6. ሁሉም ተጫራቾች 100,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ በ CPO፣ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና / በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና ጥሬ ገንዘብ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል ። 
  7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው፡፡ 
  8. በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም። 
  9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በ CPO በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ Performance bond guarantee) 10% ) ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ወስጥ ውል አስሮ በዶክመንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል፡ 
  10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስት ግዥ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ
  11. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክመንት ተቀባይነት የለውም፡፡ 
  12. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው፡፡ 
  13. ጽ/ቤቱ ጨረታውን እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀነው፡፡
  14. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል፡፡ 
  15. ፅ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው:: 

አድራሻ ፡- ትግራይ መቐለ

መቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት 

ስልክ ቁጥር 0344407335/0914755845 

የመቀለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo