የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2012 ዓም በጀት ዓመት የሚያገለግል ሃንድ ቱልስ (Plumbing Hand Tools & Electro-Mechanical Tools) ግዥ አወዳድሮ በግልፅ ጨረታ መግዛት ይፈልጋል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት

ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን:   ጥቅምት 21/2012    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን : በ30ኛዉ ቀን በ 4:00 ሰዓት ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን:  በ30ኛዉ ቀን በ 4:30 ሰዓት                                        

  1. የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው፣ 
  2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻው ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ፣ 
  3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ) በመከፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ሥራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ። 
  4. ጨረታ ዶክሜንቱን ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ። 
  5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 
  6. ሁሉም ተጫራቾች 40,000.00 የጨረታ ማስከበርያ በCPO፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ፣ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል። 
  7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው። 
  8. በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም። 
  9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ፡ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል፣ 
  10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጪ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዥ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ 
  11. የጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣ የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም። 
  12. ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው። 
  13. ጽ/ቤቱ ጨረታውን እንደ አስፈላጊነቱ ከያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  14. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት 
  • 14.1 ቴክኒካል እንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም 
  • 14.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል። 

15. ጽ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

  • አድራሻ ፦ ትግራይ መቐለ 
  • ስልክ ቁጥር፡- 0344407335 /0914755845 

መቕለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo