የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2012 ዓ/ም በጀት ዓመት የሚያገለግል ጀነሬተር ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት

ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ግዜ ጥቅምት 9 /2012  : ጨረታዉ የሚዘጋባት ቀን እና ሰዓት በ30ኛዉ ቀን 4:00 ሰዓት  ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን እና ሰዓት  በ30ኛዉ ቀን 4:30 ሰዓት                    

  1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው
  2.  ቫት የተመዘገቡና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ
  3. የጨረታው ዶክመንት የማይመለስ 200(ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መቐለ ውሃ አግልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክመንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ ።
  4. የጨረታ ዶክመንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 400 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ።
  5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 30ኛው ቀን 400 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4:30 ሰዓት ተጫራች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  6. ሁሉም ተጫራቾች 50,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ cpo በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
  7. የተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክመንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።
  8. በዶክመንቱ ከተሰጠው ስፔስፊኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም።
  9.  የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሽነፈው ዋጋ በCPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበርያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክመንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል
  10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛበት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ  ደብዳቤ እንደምንፅፍ ፣
  11. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክመንት ተቀባይነት የለውም፡፡
  12. ጨረታውፀንቶ የሚቆየውጨረታውከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው፡፡
  13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  14. የሚቀርበው ጨረታ ዶክመንት
    • 14.1. ቴክኒካል አንድ አርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም
    • 14.2. ፋይናንሺያል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል።
  15.  ጽ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ስልክ ቁጥር፦0344407335 /0914755845

አድራሻ ፡- ትግራይ መቐለ

የመቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት

Company Info

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo