የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት የሚውሉ የቢሮ ዕቃዎች እና ሌሎች አላቂ ዕቃዎች ግዥ ለመግዛት ሕጋዊ ከሆኑ አቅራቢዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

ኣፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት
  • ጨረታዉ በኣዲዝ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን:  7/2/2012
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን : ለተከታታይ 10 ቀናት ቀን ከረፋዱ 300 ሰዓት
    ጨረታዉ የመኪፈትበት ቀን : ለተከታታይ 10 ቀናት ቀን ከረፋዱ 4:00 ሰዓት
  • የቢሮ ዕቃዎች እና ሌሎች አላቂ ዕቃዎች

ስለዚህ በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

  1.  በዚህ ግልጽ ጨረታ የሚወዳደሩ አቅራቢ ድርጅቶች በ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና ምዝገባ ሠርተፍኬት ማቅረብ አለበት።
  2. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የመወዳደሪያ ሃሳብ ኦርጅናሉን በአንድ ፖስታ ኮፒውን በአንድ ፖስታ የተጫራቾቹ ስምና ፊርማ አድራሻበግልፅ ተፅፎባቸው ሁለቱም ፖስታዎች በአንድፖስታ ተደርጎበሰምታሽጎ መቅረብ ሲኖርበት ለሚጫረቱት ዕቃዎች ዓይነት እና መጠን ስዕላዊ መግለጫ የሚያስፈልገው ከሆነ በከለር የታተመ ስዕላዊ መግለጫ በፖስታ ውስጥ ተደርጎ በተወሰነው ጊዜና ሰዓት በአፋር ብ/ክ/መንግሥት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ስግዥና ፋይ/ንብ/ አስ/ደጋፊ ሥራ ሂደት ቢሮ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
  3. የሚገዙት ዕቃዎችን ዓይነት እና ዝርዝር መግለጫ (Specification) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
  4.  ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) ከፍለው ከአፋር ሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ደጋፊ ሥራ ሂደት ቢሮ መውሰድ ይችላሉ።
  5. የተዘጋጀው ጨረታ ዝርዝር ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ለተከታታይ 10 (አስር) ቀናት እስከ ይከፈታል። ጠዋቱ 3፤00 ሰዓት ድረስ ገዝተው በዚያው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ባሉበት ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ደጋፊ ሥራ ሂደት ቢሮ ይከፈታል፡፡ 
  6. ተጫራቶች ሰነዱን ገዝተው በመሙላትእናበማዘጋጀት ኦሪጅናል የመወዳደሪያ ሃሳብ ዶክመንታችሁን በአንድ ፖስታ ውስጥ በሰም በማሸግ ኮፒውን በሌላ ፖስታ ውስጥ በሰም በማሸግ በማስገባት ሁለቱንም ፖስታዎች በአንድ ፖስታ አድርጎ በሰም አሽገው ለዚሁ ግዥ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  7. ቢሮው ሊገዛው ያቀረበው የዕቃ ዝርዝር ተጫራቶቹ ለሚሸጧቸው ዕቃዎች ስዕላዊ መግለጫ የሚያስፈልገው ከሆነ በከለር የታተመ ስዕላዊ መግለጫ ማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
  8. ሻጭ ንብረቱን በንብረት ክፍል ድረስ ወስዶ ካስረከበ በኋላ በስሙ ሞዴል 19 አስቆርጦ ሂሳብ ክፍል በመውሰድ ሂሳቡን ማወራረድ አለበት።
  9. አሸናፊው ድርጅት የአሸነፈበትን ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች በራሱ ትራንስፖርት ቢሮአችን ንብረት ክፍል ማስረከብ አለበት።
  10. የጨረታው መክፈቻ ጊዜ እና ቀን የጨረታውን ፕሮግራም ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙ ሲቀሩ የጨረታውን መክፈቻ ሂደት አያስተጓጉልም።
  11. ቢሮው ጨረታውን የተሻለ አማራጭ ካገኘ በሁሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  12. ማንኛውም የጨረታ ተወዳዳሪ ለሚያቀርባቸው ዕቃዎች ብ 20,000.00 (ሃያ ሺ) የጨረታ ማስከበሪያ ድ ቦንድ (CPO) ከመወዳደሪያ ሃሳብ ማቅረቢያ ጋር በፖስታ ታሽጎ ማቅረብ አለበት።

በተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለግዎት በቢሮው ስልክ ቁጥር፡- 033-666-05-02 ደውለው ይጠይቁ፡፡

የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት

ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo