የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ከዚህ በታች የተጠቀሱት የተለያዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ማለትም፡ሰው ሠራሽ የእንስሳት ማዳቀያና መገልገያ መሣርያዎች፣ ሰው ሠራሽ የእንስሳት ማዳቀያ ማሽን መስዋወጫ እቃዎች፣ የእርሻ መገልገያ መሣርያዎች፣ የጓሮ አትክልት፣ ጀኔረተር፣ ዲናሞ፣ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ
  • ሎት 1 ሰው ሠራሽ የእንስሳት ማዳቀያና መገልገያ መሣርያዎች፣ 
  • ሎት 2.ሰው ሠራሽ የእንስሳት ማዳቀያ ማሽን መስዋወጫ እቃዎች ፣ 
  • ሎት 3. የእርሻ መገልገያ መሣርያዎች፣ 
  • ሎት 4. የጓሮ አትክልት፣ 
  • ሎት 5 ጀኔረተር፣ 
  • ሎት 6. ዲናሞ፣ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል::

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶኩሜንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 2 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል:: 

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የVAT ሠርቲፊኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና ያለፈው ወር ቫት (VAT) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት። 
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው። 
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰውን መጠን ገንዘብ በ(CPO) አሠርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል። 
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው-የዕቃዎች ብዛት እስከ 20 የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 
  • ጨረታው ጥቅምት 24/2012 ዓም ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ይከፈታል። 
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 034 440 36 63/ 034 440 43 46 ወይም በፋክስ ቁጥር 034 440 99 71/034 440 36 63 መጠየቅ ይቻላል። 

የትግራይ ክልል ግብርናና 

ገጠር ልማት ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo