የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ በ2012 ዓ.ም ለቢሮው አገልግሎት የሚውሉ ኦፊስ ፈርኒቸሮችንና ኤሌክትሮኒክሶችን በድጋሚ በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

የኣፋር ትምህርት ቢሮ

ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣበት ቀን  4/2/2012

ጨረታዉ ሚዘጋበት ቀን በ15 ኛዉ ተከታታይ  የስራ ቀናት

ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን በ 16 ኛዉ የስራ ቀን በ3:00 ሰዓት

ኦፊስ ፈርኒቸሮችንና ኤሌክትሮኒክሶችን በድጋሚ በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አቅራቢዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

1 በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ እና የግብር (ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣

2 የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡመሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣

3 ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-5 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣

4 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 ( ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ሠመራ ትም/ቢሮ ቁጥር 6 የጨረታውን ሰነድ በመግዛት የሚወዳደሩበትን ሀሳብ እና ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዶችን በመለየት በ2 ኮፒ ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

5 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፣

6 ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ትምህርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ዳሬክቶሬት ክፍል ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፣

7 ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በትምርት ቢሮ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 6 በ16ኛው የስራ ቀን በ3፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡

8 መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣

9 በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 5 በስልክ ቁጥር 033-666-0125/0920 00 91 09 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት

ትምህርት ቢሮ

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo