በኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር የመቐለ ቅ/ጽ/ቤት የሰራተኞች መኪና ሰርቪስ እና የሙሉ ቀን የመኪና ኪራይ አገልግሎት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የአገልግሎት ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን
  • ሎት አንድ የሰራተኞች መኪና ሰርቪስ እና የሙሉ ቀን የመኪና ኪራይ አገልግሎት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል። 
  1. ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ። 
  2. የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ። 
  3. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለሥልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ። 
  4. የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,00.00 /አስር ሺህ/ ብር በባንክ በተመሠከረለት ቼክ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ ። 
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ደደቢት ማይክሮ ፋይናንስ አጠገብ የሚገኘው የትግራይ አካል ጉዳተኞች ማህበር ህንፃ ከሚገኘው የቅ/ጽ/ቤቱ የግዥና ፋይናንስ ቡድን ግራውንድ ላይ ቢሮ ቁጥር 37 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ። 
  6. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጥቅምት 20 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት በመስሪያ ቤቱ አዳራሽ ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 
  7. የጨረታው አሸናፊ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና 10% (አስር በመቶ) CPO በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል። 
  8. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

ስልክ ቁጥር 0344-41-1005/09140004-78/ ፋክስ 0344407309/ 

በኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር 

የመቐለ ቅ/ፅ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo