በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የመቀሌ ቅ/ጽ/ቤት የሁመራ ጉም/ መቅ ጣቢያ የህንፃ መሳሪያዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅና በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን

ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን በጋዜጣ የወጣበት ቀን  2/2/2012

 ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን  ኣስራ አምሰተኛዉ ቀን

ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን  16ኛ ቀን 3:30                                                                                                                                                                                                         

  1.  በጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ከሚሸጠው ዕቃ ጋር ተዛማጅነት ያለው የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ክሊራንስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ እንቅስቃሴያቸውን ያሳወቁበት በቅርብ ጊዜ የተሰጣቸው የምስክር ወረቀት እና መለያ ቁጥሩን ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዞ ስኢንቨሎፕ በማሸግ ለዝግ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ያለበት ሲሆን ለግልፅ ጨረታው ደግሞ በጨረታው ዕለት ይዞ መምጣት ይኖርበታል፡፡ 
  2. ተጫራቾች የዝግ ጨረታውን ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ከ2:00-6:00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከ9:00-12:00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ጧት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመከፈል በመቅረጫ ጣቢያው በመሄድ ይህ ጨረታ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ አስራ አምስተኛው ቀን መዝጊያው ቀን ድረስ የጨረታ ሰነድ መግዛት የሚችሉ ሲሆን የግልፅ ጨረታው ደግሞ በነፃ ማግኘት ይችላሉ፡፡ 
  3. በዝግ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ ሃያ በመቶ (20%) እንዲሁም ለግልፅ ጨረታ ለቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመጫረት ብር 10.000 /አስር ሺህ ብር ብቻ ለጨረታ ዋስትና /CPO/ በሁመራ ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ ስም በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ 
  4. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት /ስኬጁል / መሰረት መጫረት ይችላሉ 

    ተ ቁ

    የቅ/ፅ/ቤቱ ስም

    የጨረታው ዓይነት

    የንብረት መመልከቻ ቀን ጋዜጣ

    ከወጣበት ቀን ጀምሮ

    የጨረታው መዝጊያና የመክፈቻ ቀን ሰዓት

    1

    ሁመራ

    ግልፅ

    ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን

    ጀምሮ እስከ አስራ አምስተኛው ቀን

    ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት

    ቀን ጀምሮ 16ኛ ቀን 3፡30

    ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል

    ዝግ

    ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን

    ጀምሮ እስከ አስራ አምስተኛው ቀን

    ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት

    ቀን ጀምሮ 16ኛ ቀን 3፡30

    ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል

  5. የጨረታው መክፈቻ ቦታ በሁመራ ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ወይም በታዛቢዎች ፊት ይከፈታል፡፡ 
  6. ለጨረታው አሸናፊ ተጫራች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት /CPO/ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ የጨረታው ውጤት ከተገለፀ በ3 ቀናት ውስጥ ተመላሸ ይደረግላቸዋል፡፡ 
  7. አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸውን በደብዳቤ ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ በ10ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ገንዘብ ገቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ 
  8. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ዋጋ ከፍያ ከፈፀሙ በ10 ቀናት ውስጥ ንብረቱን ተረክበው ማንሳት ይኖርባቸዋል፡፡ 
  9. ከላይ በተ/ቁ 7 እና በተ/ቁ 8 በተገለፁት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረገ እና ንብረቱን ተረክቦ ያልወሰነ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት እና ለንብረቱ የከፈሉት ዋጋ ለመ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡ 
  10. የጨረታው አሸናፊ ከጉምሩክ ንብረቱን ከተረከበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 3 ተከታታይ ቀናት ወደ ንግድ መደብሩ /መሸጫ ቦታው/ ንብረቱን መውሰድ አለበት፡፡ 
  11. ባለስልጣኑ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥሮች ፡- ሁመራ 034-448-00-04 /034-248-50-65 ዋ/መቤት 011 878 72 75 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ 

የተቋሙን ዌብ ሳይት WWW.ERCA.GOV.ET መመልከት ይችላሉ፡፡ 

ሁ/ጉ/መቅ/ጣቢያ ጽ/ቤት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo