በአገር መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜን ዕዝ የ33ኛ ክ/ጦር መምሪያ በ2012 በጀት ዓመት ለክ/ጦራችን ስራ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ አይነት ቋሚና አላቂ የቢሮ የፅህፈት መሳሪያ እቃዎችን፣ የተለያዩ አይነት አላቂ የፅዳት እቃዎችን፣ አቡጀዲ እና ሻሽ፣ የህሙማን ማገገሚያ ቀለብ፣ የማሽነሪ እና የጀነሬተር መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የኤሌከትሮኒከስ እና የኦፈስ ማሽን መለዋወጫ ዕቃዎች እና የቀላል ተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

በሀገር መከላከያ ሚኒስትር የሰ/ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ
  • የተለያዩ አይነት ቋሚና አላቂ የቢሮ የፅህፈት መሳሪያ እቃዎችን፣
  • የተለያዩ አይነት አላቂ የፅዳት እቃዎችን፣
  • አቡጀዲ እና ሻሽ፣
  • የህሙማን ማገገሚያ ቀለብ፣
  • የማሽነሪ እና የጀነሬተር መለዋወጫ ዕቃዎች፣
  • የኤሌከትሮኒከስ እና የኦፈስ ማሽን መለዋወጫ ዕቃዎች እና
  • የቀላል ተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ስለዚህ ጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራ በሙሉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላችሁ የዘመኑ ግብር የከፈላችሁ መሆናችሁን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የምትችሉ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባችሁ። ተጫራቾች የማስረጃችሁን ፎቶ ኮፒ በማቅረብ የእቃዎችን ዝርዝር የያዙ ሰነድ የማይመለስ ብር 50.00 በፊደል /ሃምሳ ብር መከፈል ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በ33ኛ ክ/ጦር ጎንደር አዘዞ ወታደራዊ ካምፕ ግዥ ስሮ ቀርባችሁ መግዛት ትችላላችሁ። ተጫራቾች ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ ብር 7,000 ፊደል ሰባት ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በካሽ ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ተጫራቶች እያንዳንዱ የእቃ ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ማስታውቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመግዛት በቢሮው ወደተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ጨረታው ጥቅምት 17/02/2012 ዓ/ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው ሰከፊልም ሆን ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

ለበለጠ መረጃ 0939-21-98-70 ወይም 09-40-96-52-25 

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የ33ኛ ክ/ጦር መምሪያ 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo