የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2012 ዓ/ም በጀት ዓመት የሚያገለግል ኤሌክትሪካል ሳብመርሲብል ፓምፕ ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት
  1. ጨረታዉ በኣዲስ ዘመን በጋዜጣ የወጣበት ቀን :  27/1/2012
    ጨረታዉ የሚዘጋበት ቀን : በ 30ኛዉ ቀን 4:00 ሰዓት
    ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን : በ 30ኛዉ ቀን 4:30 ሰዓት
  2. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው
  3.  ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ
  4. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 200(ሁለት መቶ) በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክመንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 3 መግዛት ይችላሉ
  5. ጨረታ ዶክመንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  6. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 30ኛው ቀን 400 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 430 ሰዓት ተጫራች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  7.  ሁሉም ተጫራቾች 50,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ CPO በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ፣ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
  8.  ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክመንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።
  9. በዶክመንቱ ከተሰጠው እስፔስፊኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም፡፡
  10. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክመንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል
  11. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና  ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንጽፋለን፡፡
  12. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣው የጨረታ ዶክመንት ተቀባይነት የለውም፡፡
  13.  ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው።
  14. ጽቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  15.  የሚቀርበው ጨረታ ዶክመንት፡
    • 14.1 ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም
    • 14.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል፡፡
  16.  ጽ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ፡- ትግራይ መቐለ

 ስልክ ቁጥር 0344407335/0914755845

የመቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo