በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል ሰርቪስና አቅም ግንባታ ቢሮ በ2012 መደበኛ በጀት የተለያዩ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

የኣፋር ሲቭል ሰርቪስና ኣቅም ግንባታ ቢሮ
  • አላቂ የቢሮ ዕቃዎችንና
  • የኮምፒውተር አክሰሰሪዎች፣
  • የኔት-ወርክ ዕቃዎች፣
  • ቋሚ ዕቃዎች
  • ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር እና ፕሪንተር ላፕቶፕ
  • ኮምፒውተር የእንግዳ ማረፊያ ወንበር የባለሙያ ወንበር እና
  • ጠረጴዛ የማናጀር ወንበር እና ጠረንጴዛ ባለ3 እና ባለ4 ተከፋዮች ሼልፍ
  • የመሬት ምንጣፍ ሞኬት እና መጋረጃ
  • ኤይሲ Wi 6 TP-LINK
  • ቋሚ የቢሮ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ 
  1. በዘርፉ የዘመኑ የታደሠ ንግድ ፈቃድ 
  2. ከሚፈለገው አገልግሎት ጋር የተዛመደ የንግድ ስራ ፈቃድ 
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት 
  4. በመንግስት አቅራቢነት የተመዘገበ 
  5. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ሰርተፍኬት ያለው 

  1. ተጫራቾች በየሎቱ/በሚወዳደሩበት ዕቃዎች 1% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታው አሸናፊ እንደታወቀ ለጨረታ ማስከበሪያ የተያዘው ገንዘብ ለተሸናፊዎች ይመለስላቸዋል፡፡ 
  2. በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት የጨረታውን ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዓት በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሲቪል ሰርቪስና አቅም ግንባታ ቢሮ የግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 32 የማይመለስ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡ 
  3. ማንኛውም የጨረታ ተወዳዳሪ የሚያቀርበውን የእቃዎች ዋጋ በግልጽና በማያሻማ መልኩ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ከዚህ መመሪያ ጋር በተያያዘ ዋጋ ማቅረቢያ ሰንጠረዥ የነጠላ እና የጠቅላላ ዋጋውን ካነቫቱ ሞልቶ ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች አሟልቶ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦሪጅናል እና ኮፒ በመለየት በተወሰነው ጊዜ ውስጥ ሠመራ የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል ሰርቪስና አቅም ግንባታ ቢሮ ምድር ላይ በሚገኘው የመረጃ ዴስክ ለዚህ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡  
  4. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት የሚቆይ እና በ11ኛው ቀን ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት የሚዘጋ ሆኖ በእለቱ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በይፋ ይከፈታል። ሆኖም ግን የመክፈቻው ቀን በዓል ወይም የእረፍት ቀን ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል። እንዲሁም ተጫራቹ በራሱ ምክንያት በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ሲቀር የጨረታውን መክፈት አያስተጓጉልም:: 

በሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው:: 

ለተጨማሪ መረጃ ፡- በቢሮው ስልክ ቁጥር 033-666-01-36/0137 ወይም 

በፋክስ ቁጥር 033-666-0408/06-39 ደውለው ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ። 

በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል 

ሰርቪስና አቅም ግንባታ ቢሮ 

ሠመራ


ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo