በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ በ2012 የበጀት ዓመት የጽህፈት መሳሪያ፣ የተሽከርካሪዎች ጎማ ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና የፈርኒቸር ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

አፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ
  • ሎት-1 የጽህፈት መሳሪያ
  •  ሎት-2 የተሽከርካሪዎች ጎማ
  •   ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ እና
  •  ሎት 4 የፈርኒቸር ግዥ ለመፈጸም በመስኩ የተሰማሩ አቅራቢዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣
  5. ተጫራቾች ለሚያቀርቡት እቃ ዝርዝር መግለጫ ወይም አስፈላጊውን መረጃ ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ የማይመለስ ብር 50 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከግዥ ፋይ/ብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 06 ማግኘት ይችላሉ፣
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላ ዋጋ 1% (አንድ ከመቶ) በባንክ ትእዛዝ (ሲ.ፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በ1 /አንድ/ ኦርጅናልና በሁለት ኮፒ በማድረግ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግዥ ፋ/ንብ/አስ/ደ/ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 06 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በጨረታው መዝጊያ ቀን 28/1/2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመ/ቤቱ የመዝናኛ ክበ በ28/1/2012 ዓ.ም በ4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  10.  መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ ተጠበቀ ነው፣
  11.  በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ቢሮ የግዥ ፋ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስል ቁጥር፡- 033 666 00 44 በመደወል ወይም በፋክስ ቁጥር፡- 033 666 04 00 በመላክ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo