የኢትዩጰያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሃገር አቀፍ ኤሌክተሪክ አቅርቦት ፕሮግራም የትግራይ ክልል ጽቤት ለፕረሮጀክት አገልግሎት የሚዉል ደብል ካፕ ተሽክርካሪዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለአንድ ዓመት ለመከራየት ይፈልጋል

በኢትዩጽያ ኤሌክትሪክ ሃይል አ/አ/ኤ/አ ፕሮጀክት ትግራይ ክልል ቤሮ

በመሆኑም በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች

1 በዘረፉ የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸዉ

2 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸዉ

3 የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ

4 ተጫራቾች ዓመታዊ የቴክኒክ ምርመራ ያከናዉነበትና የተሽከርካሪዎች የኢንሹራንስ ዋስትና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ

5 ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ተቁ 1-4 የተጠቀስቱን ከሚመለከታቸዉ መረጃ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነድ ጋር አያያዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ

6 የሚሰራዉ የስራ ዓይነት ዝርዝር መግለጫ ከጨረታዉ ሰነድ ማግኘት ይቻላልፀ

7 ተጫራቾች ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ጨረታዉ በጋዜጣ  ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት በስራ ሰዓት ማግኘት ይችላሉ

8 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለጨረታ እንዲያቀርቡት የተሽከርካ ብዛት ማለትም 1-3 ተሽከርካሪዎች የሚቀርቡ ከሆነ 15,000 /አስራ አምስት ሺ ብር/ ከ1-2 ተሽከርካሪዎች የሚቀርቡ ከሆነ 10,000 /አስር ሺ ብር/ አንድ ተሽከርካሪዎች የሚቀርቡ ከሆነ 5000 / አምስት ሺ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ CPO ወይም ቼክ ብቻ ለ UEAP Tigray Regional ተከፋይ የሆነ ጨረታ ሰነዳቸዉ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

9 ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ላይ ስማቸዉንና ፊርማቸዉ ሙሉ አድራሻቸዉን በትክክል መግለፅ አለባቸዉ

10 ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸዉ ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦርጅናል ና ኮፒ ጨረታ ቁጥር UEAP/TG/01/2008 የሚል ምልክተ በማድረግ የሃገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም የትግራይ ክልል መቐለ ጽ/ቤት ጨርቆስ ዳዊት ህንፃ ቢሮ ቁጥር 13 ለዚህ ጨረታ በተዘጋጀዉ ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል

11 የጨረታ ሳጥን ከታሸገ /ከተዘጋ በኃላ ለሚደርስ ማንኛዉም ሰነዱ ሳይከፈት ለተጫራቹ ይመለስለታል

12 ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት / ባይገኙም ጨርቆስ ዳዊት ህንፃ ቢሮ ቁጥር 13 ይከፈታል

13 የፕሮግራሙ ጽቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

14 ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0344-412078 / 0344-408062 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ

 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo