መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በመቐለ ድህረ ሽያጭ ማእከል ፕሮጀክት የመኪና ማጠቢያ ወይም ላቫጆ (Car wash) በጨረታ አወዳድሮ ለማስራት ስለሚፈልግ በኮንስትራክሽን ዘርፍ

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በመቐለ ድህረ ሽያጭ ማእከል ፕሮጀክት የመኪና ማጠቢያ ወይም ላቫጆ (Car wash) በጨረታ አወዳድሮ ለማስራት ስለሚፈልግ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ደረጃ GC-6 ወይም BC-6 እና ከዝያ በላይ ብቃት ያላችሁ እና ከዚህ በታች የተዘዘሩትን መስፈርት የምታሞሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባነያችን ይጋብዛል::

የጨረታ መስፈርት

1 ተጫራቾች ቫት (VAT) ተመዝጋቢ እና የ2006 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ መሆነ አለባቸዉ::

2 ተጫራቾች የማይመለስ አንድ የታደሰ የንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ፎቶ ኮፒ በማያያዝ የጨረታ ዋጋ በሰም በታሸገ ፖስታ ይህ ማስታውቅያ ከወጣበት ከ 17/08/2014 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 25/08/2014 እ.ኤ.አ 8:00 ሰአት (ከሳት በሆላ) መቐለ ዋና መስራያ ቤት ወይም አዲስ አበባ ቅርንጫፍ መስራያ ቤት ለዙ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባችዋል::

3 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ CPO ብር 10,000.00 (አስር ሺ ብር) በስም በታሸገ ፖስታ ከጨረታ ጋር ማስገባት አለባቸው :: በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ( CPO) ወይም ጥሬ ገንዘብ ተቀባይነት የለዉም::

4 ጨረታዉ 25/08/2014 እ.ኤ.አ ከሳት በሆላ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በ 26/08/2014 እ.ኤ.አ ከሳት በሆላ ከቀኑ 8:30 ተጫራቶች ወይም ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በ መቐለ መስፍን ዋና መ/ ቤት በሚገኝ የስብስባ አዳራሽ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸዉ የተሞላ ባይገኙም ጨረታ ሰነዱ ይከፈታል :: የስራዉ ዝርዝር ከፈለጉ የማይመለስ ብር 100 ( አንድ መቶ ብር ) በመክፈል ከመቐለ ዋናዉ ቢሮ ወይም ከአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ቢሮ መዉሰድ ይችላል::

5 ተጫራቾቸ የሚያስ ገቡት ዋጋ ቫት ( VAT) ጨምሮ መሆኑና መጠቀስ አለበት :: ይህ ካልሆነ ያስገቡት ዋጋ ቫት ((VAT) እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል ::

6 ተጫራቶች የሚያስገቡት ዋጋ ለስራዉ የሚያስፈልጉ ሁሉ (የሰዉ ሃይል " ማሽነሪና " የግንባታ ማተርያል ያጠቃለለ መሆን አለበት ::

7 ጨረታዉን አሽንፈዉ ዉል ፈፅመዉ ሳይት ከተረከቡበት ዕለት ጀምሮ በ30 ቀናት ዉስጥ ስራዉን አጠናቐዉ ማስረከብ አለባቸዉ :: ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበርያ ይስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሁኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል ::

8 ተጫራቶች ለጨረታ አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ የቴክኒካል እና ፋይናንሽያል ፕሮፖዛል ሰነድ ለየብቻ አሽገዉ ማስገባት አለባቸዉ::

9 ተጫራቶች በሌላ ተጫራቶች ዋጋ ተመስርተዉ ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም ::

10 ተጫራቶች ይህን ስራ ካሸነፉ ለሌላ ሰዎስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት እይቻልም::

11 ኩባንያዉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በክፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነዉ::


 

አድራሻ

አዲስ አበባ መቐለ

ስልክ +251- 116298563 ስልክ + 251- 344402017

ፋክስ +251- 116298560 ፋክስ + 251-344406225


 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo