በጉምሩክ ኮምሺን የመቐለ ቅ/ጽ/ቤት ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የሰራተኞች መኪና ሰርቪስ አገልግሎት ግዥ መፈጸም ይፈልጋል

የኢትዮጸያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን
  • ሎት አንድ፣ የሰራተኞች መኪና ሰርቪስ 

በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡ 

1. ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፡፡ 

2. የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ፡ 

3. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ ፡፡ 

4. የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 /አስር ሺህ/ በባንክ በተመሠከረለት ቼክ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ፡፡ 

5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ  ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መክፈቻ ቀን ድረስ ኤስኦኤስትራንስ ኢ/ያ አጠገብ የሚገኘው የአቶ ዮሃንስ ግደይ ህንፃ ላይ የቅ/ጽ/ቤቱ ሃብት አስተዳደር/ ግዥና ፋይናንስ ቡድን ሁለተኛ ፎቅ ላይ ቢሮ ቁጥር 1 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡ 

6. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ መስከረም 20/2012 ዓም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታውም በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 በመስሪያ ቤቱ አዳራሽ ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ፡፡ 

7. የጨረታው አሸናፊ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና 10% /አስር በመቶ/ CPO በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማል፡፡ 

8. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው:: 

ስልክ ቁጥር 0342407162 / 0919068385 

በጉምሩክ ኮምሺን የመቐለ 

ቅ/ጽ/ቤት 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo