በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት - መቐለ ለ 2012 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ እቃዎች ፈርኒቸር ዕቃዎች፣ ኤሌክትሪክ እና ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ፣ ፅሕፈት መሳሪያ ዕቃዎች፣ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

መቐለ ዩንቨርስቲ
  1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱም በዘመኑ የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል። 
  2. የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርቲፍኬት ማቅረብ የሚችል ወይም በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብሳይት የተመዘገበ። 
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) የተመዘገበና የምዝገባ ሰርቲፍኬት ማቅረብ የሚችል፡፡ 
  4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል። ለጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ)  
    • ለፈርኒቸር ዕቃዎች ------ ብር 60,000.00 ሎት አንድ 
    • ለኤሌክትሪክ እና ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፡- ብር 40,000.00 ሎት ሁለት 
    • ለፅሕፈት መሳሪያ ዕቃዎች -------- ብር 50,000.00 ሎት ሦስት በባንክ የተመሰከረለት ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ የሚችል።
  5. በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል። 
  6. ማንኛውም ተጫራቾች ለአንድ ሎት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ለዚሁ የተዘጋጀ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ። 
  7. ማንኛውም ተጫራቾች ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢተዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት - መቐለ ዋና ግቢ ቢሮ ቁጥር 219 መውሰድ ይችላሉ።
  8. ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 22ኛው ቀን 3፡30 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ተብሎ የተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። 
  9. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀንና ወር ጀምሮ በ22ኛው ቀን ጠዋት 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልፅ ይከፈታል። በ 22ኛው ቀን በዓል ከሆነ ደግሞ በሚቀጥለው የስራ ቀን ተመሳሳይ ሰዓት ላይ ይከፈታል። 
  10. ጨረታውን አሸንፎ በወቅቱ ውል ለማያስር የጨረታ አሸናፊ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ቢድ ቦንድ አይመለስለትም። ኢንስቲትዩቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

ለበለጠ መብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 034 441 2807 /034 441 9039 ደውሎ ማነጋገር የሚቻል መሆኑ በማሳሰብ ጭምር ነው። 

የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo