በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት፤ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት ለማከናወን ካቀዳቸው ግዥዎች ውስጥ የእንስሳት መድሀኒቶች እና የጸረ-ተባይ ኬሚካል ግዥ በአገር ውስጥ ገበያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

አፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የእንስሳት፤እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ
  • የእንስሳት መድሀኒቶች እና የጸረ-ተባይ ኬሚካል ግዥ በአገር ውስጥ ገበያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። 

ስለዚህ በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራች ከዚህ በታች የተገለጹትን ነጥቦች ማሟላት ይኖርበታል፡፡ 

1. ተጫራቾች ግዴታ ማሟላት ያለባቸው የቅድሚያ መወዳደሪያ መስፈርቶች ማለትም፡-

1.1. በዘርፉ የዘመኑ የታደሠ ንግድ ፍቃድ ያለው 

1.2. የእንስሳት መድሀኒት ንግድ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ያለው 

1.3. የንግድ ፍቃድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ያለው 

1.4. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ 

1.5. የግብር ክፍያ መለያ ቁጥር/TIN No./ ያለው 

1.6. ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ አለበት እና 

1.7. የጨረታ ሰነድ ግዥ የፈጸመ 

2. በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ 

በአዲስ ከዘመን ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታውን ሰነድ ከአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት፣ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ በግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ብር 100.00/አንድ መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ። 

3. ተጫራቾች በእያንዳንዱ በሚያቀርቡት የጨረታ ሰነዶች ላይ ተጫራቾች ወይም የህጋዊ ወኪል ፊርማና ማህተም ማኖር ይኖርባቸዋል።

4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /Bid Bond/ ለውድድር የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 1% በሲፒኦ(CPO) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል። የጨረታው ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ከተሸነፈ ለዋስትና ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናና እንዲሁም ናሙና የጨረታው ውጤት ታውቆ ውል ከተፈራረሙ በኋላ ወዲያውኑ ማስከበሪያ ይመለስላቸዋል። 

5. ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርቡት የውድድር ጥያቄ መ/ቤቱ አይቀበልም። 

6. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ15ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰአት የጨረታ ሳጥኑ የሚዘጋ ሲሆን በዕለቱ 4፡30 ሰአት በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእንስሳት፤ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 

7. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

8. ለተጨማሪ መረጃ በቢሮ ግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ዳይሮክቶሬት ክፍል በቢሮ ቁጥር 108 በአካል በመገኘት ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ። 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo