መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃላ/ የተ/የግል ኩባንያ የተለያዩ የመኪና ስፔር ፓርት በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ስለሚፈልግ ብቃት ያላችሁ እና ከዚህ በታች የተዘረዝሩትን መስፈርት የምታሟሉ ተወዳዳሪዎችን እንድትሳተፉ ኩባንያውን በኣክብሮት ይጋብዛል።

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኋ/የተ/የግ/ማህበር

1 ተጫራቾች በዘርፉ የ2011ዓ/ም የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው : የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ቫት ማሳወቂያ ኦርጂናል እና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ የጨረታው ሰነድ በስራ ሰኣት ከመቐለ ዋና ቢሮ ዳይሬክተር ኢንቨንተሪ እና ሳፕለይ ወይም ኣ/ኣበባ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት መውሰድ ይችላሉ።

2 ተጫራቾች የጨረታው ዋጋ በሰም በታሸገ ፖስታ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ከ 04/09/2019 እ.አ.አ ጀምሮ እስከ 26/09/2019 እ.ኤ.አ ከሰኣት በኃላ 8:00 ሰዓት ጀምሮ መቐለ ዋና መስሪያ ቤት ወይም ኣዲስ ኣበባ ሳሪስ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ለዚህ ተብሎ በታዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።ከሰኣቱ በኃላ ከቀኑ ልክ 8፡00 ሰኣት ካለፈ የሚመጣ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡

3 ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (CPO) 50,000.00 (ሃምሳሺ ብር) በስም በታሸገ ፖስታ ከጨረታ ጋር ማስገባት አለባቸው :: በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ እንዲሁም ጥሬ ገንዘብ ተቀባይነት የለዉም።

4 ጨረታዉ 26/09/2019 እ.አ.ኣ ከሰኣት በ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በ 26/09/2019 እ.ኤ.አ ከሰኣት በኃላ 8:30 ሰዓት ተጫራቶች ወይም ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በመቐለ መስፍን ዋና መ/ቤት በሚገኝ የስብስባ አዳራሽ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸዉ የተሞላ ከሆነ ባይገኙም ጨረታ ሰነዱ ይከፈታል።

5 ተጫራቾቸ የሚያስገቡት ዋጋ ቫት (VAT) ጨምሮ መሆኑና ወይም አለመሆኑን መጠቀስ አለበት ::ይህ ካልሆነ ያስገቡት ዋጋ ቫት (VAT) እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል።

6 ተጫራቾች የትራንስፖርት የመጫኛና መዉረጃ በተጫራቾች የሚሸፈን ይሆናል

7 ኣሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ ቀን ጀምሮ ከ5 እስከ 6 የስራ ቀናት ዉስጥ እቃዉን ማንሳት አለባቸዉ ኣለባቸው። ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ ኣማራጭ ይወስዳል

8 ተጫራቾች የሚሸጡ ስፔር ፓርት መለ መስፍን ኢንዳስትሪያል ድሕረ መሸጫ ኣገልግሎት ማእከል መጥተዉ ማየት ይችላሉ

9 ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት ኣይፈቀድም።

10  ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት እይቻልም::

11 ተጫራቾች ተጫርተዉ ያሸነፉት እቃዎች መስፍን ድሕር መሸጫ አገልግሎት ማእከል ድረስ መጥተዉ ማስነሳት አለባቸዉ ክፍያ በሚመለከት ደሞ ዕቃ ከመዉሰዳቸዉ ኣስቀድመዉ ሙሉ ክፍያ መክፍለ አለባቸዉ ክፍያ በሚመለከት ደግሞ ዕቃ ከመዉሰዳቸዉ ኣስቀድመዉ ሙሉ ክፍያ መክፈል አለባቸዉ

12 ኩባንያዉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በክፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነዉ:

ለበለጠ መረጃ ስ.ቁጥር መቐለ +251 -344402481  ፋክስ +251 -344406225

ኣድስ አበባ  +251 -116298563 ፋክስ +251 -116298560

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo