ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ2012 ዓ.ም ለመስቀል በዓል የሚሆን በጨረታ ቁጥር 02/2012 የመድረክ ዝግጅት ሙሉ ዲኮር እንዲቀርብለት ይፈልጋል።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

በዚህ መሰረት፡

  1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል 

  2. በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል 

  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል 

  4. ተጫራቹ (TIN) ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል 

  5. ለጨረታ ማስከበሪያ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስም እንደሚከተለው ማስያዝ የሚችል ይሆናል። 

    •  ሎት 1 ሙሉ የመድረክ ዝግጅት፡- ብር 50,000 (አምሳ ሺ ብር) 

    •  ተጫራቾች የአቅራቢነት ሰርቲፊኬት ማቅረብ አለባቸው። 

  6. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል በዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ከዓዲግራትዩኒቨርሲቲ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጽ/ት ቤት ብሎክ 13 ቁጥር 7 መውሰድ የሚችል ሲሆን ዋጋውን ማቅረብያለበት ደግሞ ከዩኒቨርሲቲው የሚሸጥ ኦርጅናል የመምርያ ሰነድ ማህተም ያለበት እና ዶክሜንት ማህተም የተጫራቹበማድረግ ስርዝ ድልዝ የሌለው ዋጋ ብቻ ነው። 

  7. የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚሸጥ ይሆናል። 

  8. ጨረታ ሳጥን የሚከፈትበት ቀን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመጨረሻ 16ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በግልፅ ይከፈታል። 

  9. ዝርዝር ስፔስፊኬሽን በድህረ ገፅ http://WWW.adu.edu.et ማግኘት ይቻላል። 

  10. ዩኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

የበለጠ ማብራሪያ፦ ስልክ ቁጥር 0344452318/0914734993 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል። 

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo