መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2012 ዓ/ም በጀት ዓመት የሚያገለግል ኤች ዲ ፒ ትቦ ( HDPE PIPES) ዲ ሲ ኣይ (ሲኣይ)፣ጂኤስ (ጂኣይ) ትቦ አና መገጣጠሚያዎች (DCI/CI, GS/GI PIPES & FITTINGS) እና የኤች ዲ ፒ መገጣጠሚያዎች (HOPEETTINGS) የተለያየ መጠን ያላቸው የውሃ ቆጣሪ ግዥ ኣወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት
  • ሎት አንድ፡- ኤች ዲ ፒ ትቦ ( HDPE PIPES) 
  • ሎት ሁለት ዲ ሲ ኣይ (ሲኣይ)፣ጂኤስ (ጂኣይ) ትቦ አና መገጣጠሚያዎች (DCI/CI, GS/GI PIPES & FITTINGS) እና የኤች ዲ ፒ መገጣጠሚያዎች (HOPEETTINGS) 
  • ሎት ሦስት፡- የተለያየ መጠን ያላቸው የውሃ ቆጣሪ ግዥ ኣወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሳተናፍ ለምትፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል፡፡ 
  1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው፣ 
  2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ፣ 
  3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ ለእያንዳንዱ ሎት 200.00 (ሁለት መቶ) በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ሥራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ፡፡ 
  4. ጨረታ ዶክሜንቱን ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30ኛው ቀን 2012 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ። 
  5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30ኛው ቀን 2012 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቶች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት  ይከፈታል። 
  6. ሁሉም ተጫራቾች ለሎት አንድ 50,000.00፣ ለሎት ሁለት 130,000.00፣ ለሎት ሦስት 120,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ በCPO፣በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረስ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የከፍያ ትዕዛዝ ፣ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ 
  7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋበግልጽ ማስቀመጥ አለበት፡፡ በተጨማሪም በጨረታ ዶኩሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመውመቅረብ አለባቸው፡፡ 
  8. በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፊኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም፡፡ 
  9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO፣በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክሜንቱ  በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል፡፡ 
  10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛበት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች የጨረታው ውጪ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዥ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ፣ 
  11. ጨረታ ሳጥን ከተዘጋ በኋላ የሚመጣው የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም፡፡ 
  12. ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው፡፡ 
  13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 
  14. ሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት 
  • 14.1 ቴከኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም 
  • 14.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል፡፡ 
  • 15. ጽ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

አድራሻ፡-ትግራይ መቐለ 

ስልክ ቁጥር፡- 0344407335/0914755845

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo