ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የፅህፈት መሳርያ ፣ የምግብ ግብአት ፣ የፅዳት እቃዎች ፣ የደንብ ልብስ እቃዎች ፣የቦቴ ውሃ ፣ትራንስፖርት ፣የኤሌትሪክ እቃዎች ፣የህንፃ መሳሪያ እቃዎች ፣የክችን እቃዎች ፣የመኪና ስፔር ፓርት ፣ ኤሌክትሮኒክስ ፣እንጨት የተለያዩ እቃዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

በዚህ መሰረት፦

1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና የታደሰ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል

2. በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል

4. ተጫራቹ TIN ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል

5. ለጨረታ ማስከበሪያ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስም እንደሚከተለው ማስያዝ የሚችል ይሆናል።

ሎት 1 የፅህፈት መሳርያ ፡- 100,000 (አንድ መቶ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 2 የምግብ ግብአት:- 150,000 (አንድ መቶ አምሳ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 3 የፅዳት እቃዎች:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 4 የደንብ ልብስ እቃዎች:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 5 የቦቴ ውሃ:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 6 ትራንስፖርት:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 7 የኤሌትሪክ እቃዎች:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 8 የህንፃ መሳሪያ እቃዎች:- 50,000 (አምሳ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 9 የክችን እቃዎች:- 100,000 (አንድ መቶ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 10 የመኪና ስፔር ፓርት:- 100,000 (አንድ መቶ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 11 ኤሌክትሮኒክስ:- 100,000 (አንድ መቶ ሺ ብር ብቻ)

ሎት 12 እንጨት:- 50,000 (ሃምሳ ሺ ብር ብቻ)

* ተጫራቾች የአቅራቢነት ሰርትፊኬት ወይም በዌብሳይት የተመዘገቡ መሆን አለባቸው።

6. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር ) በመክፈል በዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ብሎክ 13 ቁጥር 7 መውሰድ የሚችል ሲሆን ዋጋው ማቅረብ ያለበትደግሞ ከዩኒቨርሲቲው የሚሸጥ ኦርጅናል የመምርያ ሰነድ ማህተም ያለበት እና ዶክሜንት ማህተም የተጫራቹ በማድረግ ስርዝድልዝ የሌለው ዋጋ ብቻ ነው።

7. የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚሸጥ ይሆናል።

8. ጨረታው ሳጥን የሚከፈትበት ቀን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመጨረሻ 16ኛው የስራ ቀን 4:00 ሰዓት ተዘግቶበ 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በግልፅ ይከፈታል ።

9. ዝርዝር ስፔስፊኬሽን በድህረ ገፅ http://www.adu.edu.et ማግኘት ይቻላል።

10. ዩኒቨርሲቲው የተሻለ ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

ለበለጠ ማብራሪያ ፡-ስ.ቁ 0344452318 / 0914734993 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo