የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጤና ቢሮ ከታች በሎት የተጠቀሱትን እቃዎች ከህጋውያን ነጋዴዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ትግራይ ክልል ጤና ቢሮ
  1. የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር / TIN NO/ እና የታደሰ የአቅራቢዎች ሰርተፊኬት ምዝገባ ማቅረብ አለባቸው፡፡ 
  2. ለሎት 2- እና ሎት-3 የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የሰኔ ወር 2 2011 ዓ.ም ቫት ዲከሌሬሽን ማቅረብ አለባቸው፡፡ 
  3. ለሎት-1 የዘመኑ የ6 ወር ግብር የከፈሉበት ማስረጃ እና ለዘመኑ የታደሰ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡ 
  4. ለሎት 1- እና ለሎት-2 የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ /CPO/ብር 100,000 ማስያዝ አለባቸው፡፡ 
  5. ተወዳዳሪዎች ለሎት-1 እና ለሎት-3 የጨረታውን ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ለእያንዳንዱ አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ ለሎት-2 ደግሞ አርጅናልና ኮፒፋይናንሻልዶክሜንት በታሸገ ኤንቨሎፕ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በስራ ሰዓት የግዥ ስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር-42 ማስገባት አለባቸው፡፡ 
  6. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሆኖ የመክፈቻ ቀን እና ሰዓት እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ መመሪያዎች በሙሉ በሚሸጠው ጨረታ ሰነድ መመልከት ይቻላል፡፡ 
  7. ተወዳዳሪዎች ቫት ለሚመለከተው የሚያስገቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት፡፡ ካልሆን ቫት እንዳካተተ ይቆጠራል፡፡ 
  8. ተወዳዳሪዎች አሸናፊ ሁነው ከተገኙ ውል ከገቡበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር ለሎት-1 እና ለሎት-2 በ90 ተከታታይ ቀናት ሲሆን ለሎት 3 ደግሞ በ20 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡ 
  9. የጨረታ ሰነድ ዋጋ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ከፍለው ከትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የግዥ ስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር-42 በስራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡ 
  10. ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ እንዲሁም 20% መጨመር አልያም መቀነስ ይችላል፡፡ 
  11. ማነኛውም ግልፅ ያልሆነ ጥያቄ ካላችሁ ጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን ከመድረሱ ከ5 ቀናት በፊት በፅሁፍ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። 
  12. ዋጋ ፀንቶ የሚቆይበት (BID VALIDITY DATE) ለ60 ቀናት ይሆናል፡፡ 
  13. በእያንዳንዱ ንብረት አሸናፊው ይለያል በድምር ወይም በጠቅላላ አሸናፊ አይደረግም፡፡ 
  14. መስሪያ ቤታችን በሁሉም ሎቶች ለተሳተፉ ተጫራቾች 30%  ቅድመ ክፍያ/Advance payment/ ይፈቅዳል፡፡ 

ለበለጠ መረጃ የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ 

ስልክ ቁጥር፡-03-4440-47-15 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo