የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚያገለግል የውሃ ማጣሪያ ኬሚካል /ከሎሪን/ (Calcium Hypochlorite) ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሳተፍ ለምትፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል

የመቕለ ከተማ መጠጥ ዉሃ ኣቅርቦት
  1. የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው 
  2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ 
  3. የጨረታው ዶክመንት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ/ በመከፈል መቀለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክመንት ከደጋፊ ሥራ ሂደት ግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 13 መግዛት ይችላሉ። 
  4. ጨረታ ዶክመንቱን ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 2011 ዓም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ። 
  5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀንና 2011 ዓ.ም 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 
  6. ሁሉም ተጫራቾች 35,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ በCPO፣ በሁኔታ  ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና፣ በማይሻር ሌተር ኦፍ ክሬዲት የቀረበ ዋስትና፣ ጥሬ ገንዘብ፣ የተረጋገጠ ቼክ ወይም የክፍያ ትእዛዝ፣ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል። 
  7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ ስርዝ ድልዝ የሌለበት በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክመንቱ ውስጥ የተዘጋጁ ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው:: 
  8. በዶክመንቱ ከተሰጠው ስፔስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም። 
  9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በCPO፣ በተረጋገጠ የባንክ ጋራንቲ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (PerforInance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ወስጥ ውል አስሮ በዶክመንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል 
  10. በጨረታወኑ ሂደት ጨረታውን ለማዛባት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በመውረስ ከጨረታው ውጭ እንደሚሆን በመንግስት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንጽፍ
  11.  ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክመንት ተቀባይነት የለውም። 
  12. ጨረታዉ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ60 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው። 
  13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  14. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት 
  • 14.1. ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም 
  • 14.2. ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል። 

15.ፅ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀና ነው። 

አድራሻ፡- ትግራይ መቐለ 

መቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት  

ስልክ ቁጥር፡- 034407335/091475584

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo