ደደቢት ብድርና ቁጠባ አ/ማ ለድርጅቱ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዮ የኤለክሮኒክስ ዕቃዎች ብግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል:

ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም



 ስለሆነም በዚህ ጨረታ መወዳደር የምትፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መመዘኛዎች የምታሟሉ መጫረት የምትችሉ መሆናቹ እንገልፃለን::

1. የ2011 ዓ/ም ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ ምስክር ወረቀት፣ የንግድ ምዝገባ ሰርቲፊኬ (TIN) የተመዘገባችሁ መሆኑን የሚገልፅ እና የባለፈው ወር የቫት (VAT) ዲክላሬሽን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባችዋል::

2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ የሚሆን CPO  2% ለድርጅቱ ገቢ ማድረግ ይኖርባችዋል::

3. ሁሉም ተጫራቾች ጨረታ ሰነድ 8/11/2011 ዓ/ም ጀምሮ  በአዲስ አበባ ተክለሃይማኖት ቅርንጫፍና በመቐለ በሚገኘው ዋና መስሪያቤታችን ደደቢት ብድርና ቁጠባ አ/ማ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 409 አስፈላጊውን ማስረጃ በመያዝ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ዝርዝር የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ

4. ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ውስጥ ያሉ ቅፆችን በትክክል በመሙላት በየአንዳንድ ገፅ በመፈረም እና ማህተም በማድረግ ምንም ገፅ ሳያጓድሉ ማቅረብ አለባችሁ:: የጎደለ ገፅ ወይም የተዛባ ሰነድ ማቅረብ ከጨረታ ውጭ ያደርጋል::

5. ተጫራቾች የተጫረቱበትን ጀነሬተሮች ቴክኒካልና ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል አንድ ኮፒ እንዲሁም የጨረታ ማስከበርያ ሰነድ በተለያዩ ፖስታዎች በማሸግ ሁሉንም በትልቅ ፖስታ በማሸግ መቐለ ዋና ቢሮ በ4ኛ ፎቅ በተዘጋጀው ሳጥን ገቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል::

6. ጨረታው 19/11/2011 . ከጥዋቱ 300 ተዘግቶ በድርጅቱ የቀረበውን ሰነድ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት እንዲሁም የተሟላ ዶኩሜንቱ ከሆነ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በይኖሩም ከጥዋቱ 330 ይከፈታል::

7. የጨረታው አሸናፊ ውጤት እንደተገለፀ በአምስት/5/ ቀን ውስጥ ውል ማሰር ይኖርበታል::

8. የጨረታው አሸናፊ የጨረታው ውጤት እንደተገለፀ የመልካም ስራ አፈፃፀም ከጠቅላላ ዋጋ 10% የስራ አፈፃፀም ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርበታል::

9. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

10. ለበለጠ መረጃ ዋና ቢሮ ሶስተኛ ፎቅ ቁጥር 11 ወይም በስልክ ቁጥር 0342-40-00-14 መቐለ ዋና ቢሮ በመደወል ማረጋገጥ የምትችሉ መሆናችሁን እንገልፃለን::

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo