የኢትዩጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የትግራይ ኣህጉር ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት የዘላቂ ቤት የቤተክርስትያን ደን ልማትና የህ/ሰብ ኑሮ ማሻሽያ ፕሮጀክት በእንደርታ ወረዳ ለደብረማዕረነትና ማይ ኣንበሳ ቀበሌዎች ለንብ ልማት /እርባታ ግልጋሎት ስራ የሚውሉ ባለ አንድ ድራብ የዘመናዊ ቆፎ ግብኣቶች ለመግዛት ስለሚፈልግ ይህን ሊያቀርቡ ለሚችሉ ተጫራቾች በጨረታው የተዘጋጀ ዝርዝር ሰነድ /ስፔስፊኪሽን/ መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾችን ይፈልጋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮምሽን የትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት

1 የኣቅራቢነት ኣምራች ፋብሪካ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው።

2 የ201/2011 ዓ/ም ግብር የከፈሉና የዓመት ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ::

3 ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ የሆኑና ያለፈዉ ወር ተ.እ.ታ የከፈሉበት መረጃ ማቅረብ የሚችሉ::

4 ተጫራቾች ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱት መረጃዎች ኦርጂናል በመያዝ የጨረታ ሰነድ መውሰድ አለባቸው፡፡፡

5 ተጫራቾች የጨረታዉን ሰነድ የማይመለስ 20.00 / ሃያ ብር/ በመግዛት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 / አስር / ቀናት ዉስጥ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ::

6 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 3000 /ሁለት ሺ ብር / የባንክ ዋስትና ወይም CPO በተለየ ፖስታ ኣሽገው ወይም በኣካል ይዘው መቅረብ የሚችሉ::

7 ዕቃው ውል ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ ውስጥ እቃውን ፕሮጀክቱ በሚያዘው ባለሙያ ስለ ትክክለኛነቱ በማረጋገጥ ፅ/ቤታችን ማቅረብ የሚችል፤

8 ተሞልቶ የሚቀርበዉ ሰነድ በተሰጠው ስፔስፊኬሽን መሰረት ሆኖ ስርዝ ድልዝ የሌለበትና መሆን ኣለበት፤

9 የጨረታዉ ሰነድ ዋናዉና ቅጂ ለየብቻዉ በስም በታሸገ ኢንቨሎፕ ለጨረታዉ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ያስፈልጋል::

10 የጨረታዉ ሳጥን በ 15/11/2011 ዓ/ም ጥዋት 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጥዋቱ 4:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ወይም መገኘት የማይችሉ ከሆነ ሰነዳቸዉን በማሟለት በፖስታቸዉ ላይ ይከፈትልኝ ብለዉ ከፈረሙና የድርጅቱ ማህተም ካደረጉ በሌሉበት በትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ /ቤት ይክፈታል::

11 ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በክፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ::

አድራሻ 05 ቀበሌ ኮንደሚኒየም አጠገብ የኦርቶዶክስ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo