አክሱም ዩኒቨርሲቲ የምግብ ጥሬ እቃዎችና አትክልቶች ፣ የቧንቧ እና የህንፃ መሳሪያ እቃዎች /ድጋሚ/፣ ነጭ ጤፍ በዩኒቨርሲቲው ናሙና መሰረት ከህጋዊ ነጋዴዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ኣክሱም ዩኒቨርሲቲ

ተ.ቁ


የጨረታ ሰነድ ቁጥር /ሎት/

የጨረታ ዓይነት

የጨረታ ሰነድ መሸጫዋጋ

የጨረታ ማስከበርያ

1

ሎት 33

የምግብ ጥሬ እቃዎችና አትክልቶች

100.00

200,000.00

2

ሎት 34

የቧንቧ እና የህንፃ መሳሪያ እቃዎች /ድጋሚ/

100.00

6,000.00

3

ሎት 35

ነጭ ጤፍ በዩኒቨርሲቲው ናሙናመሰረት

100.00

125,000.00

ከህጋዊ ነጋዴዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

1.በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀንና ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት በዩኒቨርሲቲው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከግዥ ክፍል፣ ህንፃ ቁጥር 53፤ ቢሮ ቁጥር 002፤ ዘወትር በሥራ ሰዓት ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ ::

2.ተጫራቾች በሥራው መስክ የተሰማሩና ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው መሆኑን የሚያስረዳና በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስፈልግ ማስረጃዎች ማያያዝ አለባቸው፡፡

3.የዘመኑ ግብር የከፈሉ፣ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፣ የክልል/የፌዴራል በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆን አለባቸው::

4.ተጫራቾች በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆኑን ማስረጃ ማያያዝ አለባቸው፡፡

5.ለጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት 3% ልዩ አስተያየት ይደረጋል፡፡

6.ጨረታው የሚከፈተው የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን 15 ቀን በኋላ ባለው ቀጣይ የሥራ ቀን ሆኖ በጨረታ ሰነዱ በተገለጸው ቀንና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት በግልጽ በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ይከፈታል፡፡

7.ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ሳይኙ በመቅረታቸው የጨረታውን መክፈት አይስተጓጎልም፡፡

8.የጨረታው አሸናፊ በጊዜው ቀርቦ ውል የማያስር ከሆነ በጨረታ ሰነዱ የተገለጸው ለጨረታ ማስከበሪያነት ያስያዘው ገንዘብ አይመለስለትም፡፡

9.ዩኒቨርሲቲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡

ለተጨማሪ መረጃ፡ በስልክ ቁጥር- +251 09 14 18 91 15/09 14 19 18 46 ደውለው ይጠይቁ፡፡

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo