የትግራይ ክልል ትም/ቢሮ የተለያዩ መፅሐፍት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሳተም ይፈልጋል

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ

1 ጨረታውን በተመለከተ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለው ማቅረብ አለበት።

2 በአቅራቢነት የተመዘገበና ቲን ቁጥር ያለው መሆን አለበት። .
3 የጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ (CPO) ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) ማቅረብ አለበት።
4 ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ይህ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት መቐለ ከሚገኘውከትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ሕንፃ 1ኛ ፎቅ ግዥ ክፍል የማይመለስ ብር100.00/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይቻላል።

5 የጨረታ አሸናፊ ውል ከፈፀመበት ጊዜ ጀምሮ በ 60 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በስፔስፊኬሽንና ጥራቱ ያለውና ደረጃውን የጠበቀ ህትመት በትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ንብረት ክፍል በባለሞያ አረጋግጦ ማስረከብ ይጠበቅበታል።
6 ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ በተከታታይ እስከ 16ኛው ቀን 8፡30 ሰዓት ድረስ በትግራይክልል ትም/ ቢሮ 1ኛ ፎቅ ግዥ ክፍል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን የጨረታ ዶክመንት ማስገባት ይቻላል።
7 ጨረታው በ16ኛው ተከታታይ ቀን በ8፡45 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 9፡00 ሰዓት ይከፈታል ። 16ኛው ቀን በዓል ከዋለ ግንበ ሚቀጥለው የሥራ ቀን የመዝጊያና የመክፈቻ ቀን ይሆናል።
8 ተጫራቾች ጨረታ ዶክመንት ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው።
9 ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0344-4034-77 /0344408299 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።

ስፖንሰሮች

ሃሳቦች የሚሰራጩባቸው መንገዶች.
Milkta Logo